2 Solunjanima 3 – CRO & NASV

Knijga O Kristu

2 Solunjanima 3:1-18

Zamolba za molitvu

1I na koncu, draga braćo i sestre, molim vas da se za mene molite: da se Božja riječ brzo širi i proslavlja kao i među vama 2te da se oslobodimo pokvarenih i zlih ljudi jer svi nemaju vjere. 3Ali Gospodin je zato vjeran. On će vas ojačati i sačuvati vas od Zloga. 4Pouzdajemo se u Gospodina da činite i da ćete činiti kako smo vam zapovjedili. 5Neka vam Gospodin dade još dublju spoznaju Božje ljubavi i postojanosti u Kristu.

Ohrabrenje na dostojan život

6A ovo vam, draga braćo i sestre, zapovijedamo u ime Gospodina Isusa Krista: klonite se svakoga brata koji besposliči i ne živi prema predaji koju smo vam dali. 7Dobro znate da trebate činiti kao i mi. Dok smo bili kod vas, nismo ljenčarili 8niti smo badava jeli ičiji kruh. Danonoćno smo radili samo da ne padnemo vama na teret. 9Ne da na to nismo imali pravo, nego smo vam htjeli poslužiti kao uzor. 10Dok smo bili među vama, zapovjedili smo: “Tko neće raditi, neka i ne jede!”

11Ipak čujemo da neki od vas besposliče, da sami ništa ne rade, nego samo zabadaju nos u tuđe poslove. 12Takvima zapovijedamo u ime Gospodina Isusa Krista, štoviše zaklinjemo ih da s mirom rade i da jedu vlastiti kruh. 13A vama ostalima, braćo i sestre, neka ne dodija činiti dobro.

14Ne pokori li se tko ovoj našoj pismenoj zapovijedi, klonite ga se da se posrami, 15ali ne smatrajte ga neprijateljem, nego ga opominjite kao brata.

Pavlovi posljednji pozdravi

16Neka vam sam Gospodin mira dade mir uvijek i u svemu. Gospodin sa svima vama!

17A evo i pozdrava od mene, Pavla, napisanoga mojom rukom. Pišem ga tako u svakoj poslanici, kao znak raspoznavanja.

18Neka milost našega Gospodina Isusa Krista bude nad svima vama.

New Amharic Standard Version

2 ተሰሎንቄ 3:1-18

ለጸሎት የቀረበ ጥያቄ

1በቀረውስ ወንድሞች ሆይ፤ በእናንተ ዘንድ እንደ ሆነው የጌታ ቃል በፍጥነት እንዲሠራጭና እንዲከበር ለእኛ ጸልዩልን፤ 2ደግሞም ሰው ሁሉ እምነት ያለው ስለማይሆን ከዐመፀኞችና ከክፉ ሰዎች እንድንድን ጸልዩልን። 3ጌታ ግን ታማኝ ነው፤ እርሱም ያበረታችኋል፤ ከክፉውም ይጠብቃችኋል። 4እኛ ያዘዝናችሁን አሁን አደረጋችሁ፤ ወደ ፊትም እንደምታደርጉ በጌታ እንታመናለን። 5ጌታ ልባችሁን ወደ እግዚአብሔር ፍቅርና ወደ ክርስቶስ ጽናት ይምራው።

ሥራ መፍታት እንደማይገባ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

6ወንድሞች ሆይ፤ ሥራ ፈት ከሆነና ከእኛ በተቀበላችሁት ትምህርት3፥6 ወይም ወግ መሠረት ከማይኖር ወንድም እንድትርቁ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን፤ 7የእኛን ምሳሌ እንዴት መከተል እንደሚገባችሁ እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁና። ከእናንተ ጋር በነበርንበት ጊዜ ሥራ ፈቶች አልነበርንም፤ 8ደግሞም የማንንም እንጀራ በነጻ አልበላንም፤ ነገር ግን ከእናንተ በአንዳችሁም ላይ ሸክም እንዳንሆን ሌሊትና ቀን እንደክምና እንሠራ ነበር፤ 9ይህን ያደረግነው ምሳሌነታችንን እንድትከተሉ ብለን እንጂ የሚያስፈልገንን ነገር ከእናንተ ለማግኘት ሥልጣን ሳይኖረን ቀርቶ አይደለም። 10ከእናንተ ጋር በነበርንበት ጊዜ፣ “ሊሠራ የማይወድድ አይብላ” ብለን ይህን ትእዛዝ ሰጥተናችሁ ነበርና። 11ከእናንተ አንዳንዶች ሥራ ፈቶች እንደ ሆኑ ሰምተናል፤ እነርሱም ያለ ሥራ እየዞሩ በሰው ጕዳይ ጣልቃ የሚገቡ ናቸው። 12እንደዚህ ያሉ ሰዎች ተግተው ሥራቸውን እንዲሠሩና እንጀራቸውን እንዲበሉ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛቸዋለን፤ እንመክራቸዋለንም። 13እናንተ ግን ወንድሞች ሆይ፤ መልካም ሥራን ከመሥራት ከቶ አትታክቱ።

14በዚህ መልእክት ላይ ላለው ቃላችን የማይታዘዝ ማንም ቢኖር፣ እንደዚህ ያለውን ሰው በጥንቃቄ ተከታተሉት፤ በሥራውም እንዲያፍር ከእርሱ ጋር አትተባበሩ። 15ሆኖም እንደ ወንድም ገሥጹት እንጂ እንደ ጠላት አትቍጠሩት።

የመጨረሻ ሰላምታ

16የሰላም ጌታ ራሱ በሁሉም ነገር ዘወትር ሰላም ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።

17ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ የጻፍሁት እኔ ጳውሎስ ነኝ፤ የመልእክቶቼም ሁሉ መለያ ይህ ነው፤ አጻጻፌም እንደዚህ ነው።

18የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።