馬可福音 13 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

馬可福音 13:1-37

預言聖殿被毀

1耶穌走出聖殿的時候,有一個門徒對祂說:「老師,你看!這是多麼大的石頭,多麼宏偉的建築啊!」

2耶穌說:「你看見這宏偉的建築了嗎?將來它要被完全拆毀,找不到兩塊疊在一起的石頭。」

3耶穌面向聖殿坐在橄欖山上,彼得雅各約翰安得烈私下來問祂: 4「請告訴我們,這些事什麼時候會發生?有什麼預兆?」

5耶穌對他們說:「你們要小心,免得被人迷惑。 6將有很多人冒我的名來,說,『我是基督』,欺騙許多人。

7「你們聽見戰爭爆發、戰訊頻傳時,不要驚慌,因為這些事必然發生,只是末日還沒有到。

8「民族將與民族互鬥,國家將與國家相爭,各處將有地震和饑荒。這些只是災難13·8 災難」希臘文是「生產之痛」。的開始。

9「你們要小心,因為你們將被送上法庭,將在會堂裡受鞭打,又將為了我的緣故在官長和君王面前做見證。 10不過,福音一定要先傳遍天下。 11你們被拘捕,受審訊的時候,不用預先考慮怎樣辯解,到時候賜給你們什麼話,你們就說什麼話,因為那時候說話的不是你們自己,而是聖靈。

12「那時,人必把自己的弟兄置於死地,父親必把兒子置於死地,兒女必反叛父母,置他們於死地。 13你們將為我的名而被眾人憎恨,但堅忍到底的必定得救。

大災難

14「當你們看見『那帶來毀滅的可憎之物』站在不當站的地方時(讀者須會意),住在猶太地區的人要逃到山上去; 15在屋頂上的人不要下來,不要進房屋收拾行李; 16在田間的人不要回家取外衣。 17那時,孕婦和哺育嬰兒的母親們可就遭殃了! 18你們要祈求上帝使這些事不要在冬天發生, 19因為那是上帝創造天地以來空前絕後的大災難。 20如果主不縮短災期,恐怕沒有人能活命,但為了祂所揀選的子民,祂已經縮短災期。 21那時,如果有人對你們說,『看啊!基督在這裡』,或說,『基督在那裡』,你們不要相信。 22因為假基督和假先知將出現,行各種神蹟奇事,如果可能,甚至會迷惑上帝揀選的子民。 23你們要小心,我已經把一切預先告訴你們了。

人子降臨

24「大災難過後,

太陽昏暗,

月亮無光,

25星宿隕落,

天體震動。

26那時,世人必看到人子駕著雲、帶著極大的能力和榮耀降臨。 27祂必差遣天使從四面八方、天涯海角招聚祂揀選的人。

28「你們可以從無花果樹學個道理。當無花果樹發芽長葉的時候,你們就知道夏天快來了。 29同樣,當你們看見這些事情發生時,就知道人子快來了,就在門口。 30我實在告訴你們,這個世代還沒有過去,這一切都要發生。 31天地都要過去,我的話卻永遠長存。

32「但沒有人知道那日子和時辰何時來到,連天上的天使和人子都不知道,只有天父知道。 33你們要小心,警醒禱告,因為你們不知道那日子何時來到。

34「這就好像一個人在出遠門之前,把家中的事交給僕人,讓他們各做各的工作,又吩咐守門的人要警醒。 35所以你們要警醒,因為你們不知道主人什麼時候回來,可能是黃昏,可能是夜半,也可能是黎明或早上。 36別讓他突然回來時看到你們在睡覺。 37我勸你們也勸所有的人,要警醒!」

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 13:1-37

የመጨረሻው ዘመን ምልክቶች

13፥1-37 ተጓ ምብ – ማቴ 24፥1-51ሉቃ 21፥5-36

1ከቤተ መቅደስ ሲወጣ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፣ “መምህር ሆይ፤ ድንጋዮቹ እንዴት እንደ ሆኑ፣ ሕንጻውም እንዴት ውብ እንደ ሆነ እይ” አለው።

2ኢየሱስም መልሶ፣ “እነዚህን ታላላቅ ሕንጻዎች ታያለህን? አንዱ ድንጋይ በሌላው ላይ እንደ ሆነ አይቀርም፤ ሁሉም ፈራሽ ነው” አለው።

3ኢየሱስ በቤተ መቅደሱ ትይዩ፣ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ተቀምጦ ሳለ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ዮሐንስና እንድርያስ እንዲህ ሲሉ ጠየቁት፤ 4“ይህ መቼ እንደሚሆን ንገረን፤ የዚህስ ሁሉ ፍጻሜ ምልክቱ ምንድን ነው?”

5ኢየሱስም እንዲህ ይላቸው ጀመር፤ “ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ፤ 6ብዙዎች፣ ‘እኔ እርሱ ነኝ’ እያሉ በስሜ ይመጣሉ፤ ብዙዎችንም ያስታሉ። 7ስለ ጦርነትና ስለ ጦርነት ወሬ በምትሰሙበት ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህማ መሆን አለበት፤ ፍጻሜው ግን ገና ነው። 8ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥት በመንግሥት ላይ ይነሣል፤ በብዙ ቦታም የመሬት መንቀጥቀጥና ራብ ይሆናል፤ እነዚህ ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።

9“ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ ለአካባቢ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጧችኋል፤ በምኵራብ ይገርፏችኋል፤ ምስክር ትሆኑም ዘንድ በእኔ ምክንያት በገዦችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ። 10አስቀድሞ ግን ወንጌል ለሕዝብ ሁሉ መሰበክ አለበት። 11ተይዛችሁ ለፍርድ በምትቀርቡበት ጊዜ፣ በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ እንጂ ምን እንናገራለን በማለት አስቀድማችሁ አትጨነቁ፤ የሚናገረው መንፈስ ቅዱስ እንጂ እናንተ አይደላችሁምና።

12“ወንድም ወንድሙን፣ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፤ ልጆች በወላጆቻቸው ላይ ያምፃሉ፤ ይገድሏቸዋልም። 13በእኔ ምክንያት በሰው ሁሉ ዘንድ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻው የሚጸና ግን ይድናል።

14“ ‘የጥፋት ርኩሰት’ ስፍራው ባልሆነ ቦታ ቆሞ በምታዩት ጊዜ አንባቢው ያስተውል፤ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፤ 15በቤቱ ጣራ ላይ ያለ አይውረድ፤ ንብረቱንም ለማውጣት ወደ ቤቱ አይግባ፤ 16በዕርሻ ቦታ ያለ ልብሱን ለመውሰድ አይመለስ። 17በእነዚያ ቀናት ለነፍሰ ጡሮችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው! 18ይህም በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤ 19በመጀመሪያ እግዚአብሔር ፍጥረትን ከፈጠረበት ጊዜ አንሥቶ እስከ አሁን ድረስ፣ እንዲሁ ደግሞም ወደ ፊት አቻ የሌለው ታላቅ መከራ ይሆናልና። 20ጌታ ቀኖቹን ባያሳጥራቸው ኖሮ ማንም ባልዳነ ነበር፤ ስለ መረጣቸው ስለ ምርጦቹ ሲል ግን ቀኖቹን አሳጥሯል። 21በዚያን ጊዜ ማንም፣ ‘እነሆ፤ ክርስቶስ13፥21 ወይም መሲሑ እዚህ ነው?’ ቢላችሁ ወይም፣ ‘እነሆ፤ እዚያ ነው’ ቢላችሁ አትመኑ። 22ሐሰተኛ ክርስቶሶችና ሐሰተኛ ነቢያት ተነሥተው፣ ምልክቶችንና ድንቆችን በማድረግ፣ ቢቻላቸው የተመረጡትን እንኳ ያስታሉ። 23ስለዚህ ተጠንቀቁ፤ ጊዜው ሳይደርስ ሁሉን ነግሬአችኋለሁ።

24“በዚያን ጊዜ፣ ከመከራው በኋላ ‘ፀሓይ ትጨልማለች፣

“ ‘ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም፤

25ከዋክብት ከሰማይ ይረግፋሉ፤

የሰማይ ኀይላትም ይናወጣሉ።’

26“በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በታላቅ ኀይልና ግርማ በደመና ሲመጣ ያዩታል። 27እርሱም መላእክቱን ልኮ ከአራቱ ነፋሳት፣ ከምድር ዳርቻ እስከ ሰማያት ዳርቻ ምርጦቹን ይሰበስባል።

28“ምሳሌውን ከበለስ ተማሩ፤ ቅርንጫፏ ሲለመልም፣ ቅጠሏ ሲያቈጠቍጥ በጋ እንደ ተቃረበ ታውቃላችሁ፤ 29እንዲሁ ደግሞ እነዚህ ነገሮች መፈጸማቸውን ስታዩ እንደ ቀረበ፣ በደጅም እንደ ሆነ ዕወቁ። 30እውነት እላችኋለሁ፣ እነዚህ ነገሮች እስከሚፈጸሙ ድረስ ይህ ትውልድ13፥30 ወይም ዘር አያልፍም፤ 31ሰማይና ምድር ያልፋሉ፣ ቃሌ ግን አያልፍም።

ቀኑና ሰዓቱ አይታወቅም

32“ነገር ግን ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያችም ሰዓት ከአብ በቀር፣ የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ፣ ወልድም ቢሆን፣ ማንም አያውቅም። 33ስለዚህ ጊዜው መቼ እንደሚሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፣ ጸልዩም13፥33 ጸልዩ የሚለው ቃል በአንዳንድ ቅጆች አይገኝም። 34ይህም ቤቱን ለአገልጋዮቹ ትቶ፣ እያንዳንዱን አገልጋይ በየሥራ ድርሻው ላይ አሰማርቶ፣ በረኛው ነቅቶ እንዲጠብቅ አዝዞ የሄደውን ሰው ይመስላል። 35እንግዲህ የቤቱ ባለቤት በምሽት ወይም በውድቅት፣ በዶሮ ጩኸት ወይም ጎሕ ሲቀድድ እንደሚመጣ አታውቁምና ተግታችሁ ጠብቁ፤ 36ድንገት ሲመጣ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ፤ 37ለእናንተ የምነግራችሁን ለሰው ሁሉ እናገራለሁ፤ ተግታችሁ ጠብቁ!”