雅各書 5 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

雅各書 5:1-20

警告為富不仁者

1你們這些富有的人啊!為那將要臨到你們身上的災難痛哭哀號吧! 2你們的財物朽壞了,衣服也被蟲蛀了。 3你們的金銀生了鏽,那鏽必要指控你們,像火一樣吞噬你們的身體。在末世的日子裡,你們只知道積攢財寶。 4工人替你們收割莊稼,你們卻剋扣他們的工錢。那工錢發出不平的呼喊,工人的冤聲已經傳到萬軍之主的耳中了。 5你們在世上奢侈享樂,在被宰殺的日子裡,把自己養得肥肥胖胖。 6你們冤枉好人、殘害無辜,他們也沒有反抗。

要忍耐到底

7弟兄姊妹,你們要一直忍耐到主來。你們看農夫怎樣耐心等候地裡寶貴的出產,等候秋雨和春雨的降臨。 8同樣,你們也要忍耐,心志堅定,因為主快來了。 9弟兄姊妹,不要互相埋怨,免得受審判。你們看,審判的主已經站在門外了。 10弟兄姊妹,你們要效法從前奉主的名說話的先知,以他們的受苦和忍耐為榜樣。 11我們認為那些忍耐到底的人是有福的。你們都知道約伯的忍耐,也知道主最終怎樣待他,因為主充滿憐憫和慈悲。

12我的弟兄姊妹,最重要的是不可起誓,不可指著天起誓,也不可指著地起誓,不可指著任何東西起誓。你們說話,是就說是,不是就說不是,免得你們受審判。

禱告的力量

13你們中間正在受苦的人應該禱告,喜樂的人應該唱歌讚美, 14生病的人應該請教會的長老來,奉主的名用油抹他的身體並為他禱告。 15出於信心的禱告必能使病人痊癒,主必使他康復。倘若他犯了罪,也必得到赦免。 16所以你們要彼此認罪,互相代禱,好得到醫治。義人的禱告有極大的力量和功效。 17以利亞先知和我們一樣同是血肉之軀,他懇切地祈求不要下雨,結果三年半沒有下雨。 18後來他再禱告求雨,天就降雨,地也長出了莊稼。

19我的弟兄姊妹,如果有人領一個偏離真道的人歸回正路, 20他該知道:使一個迷途中的罪人歸回正路就是救一個靈魂脫離死亡,並且會遮蓋許多罪。

New Amharic Standard Version

ያዕቆብ 5:1-20

ለጨካኝ ሀብታሞች የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

1እንግዲህ እናንተ ሀብታሞች ስሙ፤ ስለሚደርስባችሁ መከራ አልቅሱ፤ ዋይ ዋይም በሉ። 2ሀብታችሁ ሻግቷል፤ ልብሳችሁንም ብል በልቶታል። 3ወርቃችሁና ብራችሁ ዝጓል፤ ዝገቱም በእናንተ ላይ ይመሰክራል፤ ሥጋችሁንም እንደ እሳት ይበላዋል፤ ለመጨረሻው ዘመን ሀብትን አከማችታችኋል። 4ልብ በሉ፤ ዕርሻችሁን ሲያጭዱ ለዋሉ ሠራተኞች ያልከፈላችሁት ደመወዝ በእናንተ ላይ ይጮኻል፤ የዐጫጆቹም ጩኸት ሁሉን ቻይ ወደ ሆነው ጌታ ጆሮ ደርሷል። 5በምድርም ላይ በምቾትና በመቀማጠል ኖራችኋል፤ ለዕርድ5፥5 ወይም ለድግስ ቀን ልባችሁን አወፍራችኋል። 6እናንተን ያልተቃወሙትን ንጹሓን ሰዎች ኰንናችኋል፤ ገድላችኋልም።

በመከራ ውስጥ መታገሥ

7እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ ጌታ እስከሚመጣ ድረስ ታገሡ። ገበሬ መሬቱ መልካምን ፍሬ እስከሚሰጥ ድረስ እንዴት እንደሚታገሥ፣ የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ እንዴት እንደሚጠባበቅ አስተውሉ። 8እናንተም እንዲሁ ታገሡ፤ ልባችሁንም አጽኑ፤ ምክንያቱም የጌታ መምጫ ተቃርቧል። 9ወንድሞች ሆይ፤ እርስ በርሳችሁ አታጕረምርሙ፤ አለዚያ ይፈረድባችኋል፤ እነሆ፤ ፈራጁ በበር ላይ ቆሟል።

10ወንድሞች ሆይ፤ በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያት የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ አድርጋችሁ ተመልከቱ። 11በትዕግሥት የጸኑትን የተባረኩ አድርገን እንደምንቈጥር ታውቃላችሁ፤ ኢዮብ እንዴት ታግሦ እንደ ጸና ሰምታችኋል፤ ጌታም በመጨረሻ ያደረገለትን አይታችኋል። ጌታ እጅግ ርኅሩኅና መሓሪ ነው።

12ከሁሉም በላይ ወንድሞቼ ሆይ፤ በሰማይ ወይም በምድር ወይም በማናቸውም ነገር ቢሆን አትማሉ፤ “አዎ” ቢሆን አዎ ይሁን፤ “አይደለም” ቢሆን አይደለም ይሁን፤ አለዚያ ይፈረድባችኋል።

ከእምነት የሆነ ጸሎት

13ከእናንተ መካከል በመከራ ውስጥ ያለ አለ? እርሱ ይጸልይ፤ የተደሰተ አለ? የምስጋና መዝሙር ይዘምር። 14ከእናንተ መካከል የታመመ ሰው አለ? የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ይጥራ፤ እነርሱም በጌታ ስም ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። 15በእምነት የቀረበ ጸሎት የታመመውን ሰው ይፈውሰዋል፤ ጌታም ያስነሣዋል፤ ኀጢአትም ሠርቶ ከሆነ፣ ይቅር ይባላል። 16ስለዚህ ኀጢአታችሁን እርስ በርሳችሁ ተናዘዙ፤ ትፈወሱም ዘንድ አንዱ ለሌላው ይጸልይ። የጻድቅ ሰው ጸሎት ኀይል አለው፤ ታላቅ ነገርም ያደርጋል።

17ኤልያስ እንደ እኛ ሰው ነበረ፤ ዝናብ እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፤ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ተኩል ዝናብ አልዘነበም። 18እንደ ገናም ጸለየ፤ ዝናብም ከሰማይ ዘነበ፤ ምድርም ፍሬዋን ሰጠች።

19ወንድሞቼ ሆይ፤ ከእናንተ አንዱ ከእውነት ቢስትና ሌላው ቢመልሰው፣ 20ይህን አስተውሉ፤ ኀጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልስ ሰው ነፍሱን ከሞት ያድነዋል፤ ብዙ ኀጢአትንም ይሸፍናል።