雅各書 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

雅各書 1:1-27

1我是作上帝和主耶穌基督奴僕的雅各,問候散居各地的十二支派的人。

信心和忍耐

2我的弟兄姊妹,當你們遭遇各種磨煉的時候,都要認為是喜樂的事。 3要知道你們的信心經過考驗會產生堅忍。 4你們要堅忍到底,使你們纯全、完備、毫無缺欠。

5如果你們誰缺少智慧,就當求慷慨施恩、不責備人的上帝,上帝必賜給他智慧。 6-8但他要憑信心毫不疑惑地祈求,因為疑惑的人三心二意,行事為人沒有定見,就像海上隨風翻騰的波濤,這種人從主那裡什麼也得不到。

9卑微的弟兄高升,應當快樂。 10富有的弟兄降卑,也要快樂,因為他會像花草一樣衰殘。 11驕陽升起,草就乾枯,花也凋謝,美麗就消失了。富有的人在忙忙碌碌中也會如此衰殘。

12在試煉中能夠忍耐到底的人有福了,因為他若經得起考驗,就會得到主應許賜給愛祂之人的生命冠冕。 13當人受到誘惑時,不可說:「是上帝在誘惑我。」因為上帝不受邪惡的誘惑,也不誘惑人。 14其實每個受到誘惑的人都是受自己的私慾慫恿和誘惑。 15私慾懷了胎,便生出罪,罪一旦長成,便帶來死亡。

16我親愛的弟兄姊妹,不要上當受騙。 17一切良善的施予和完美的恩賜都是從天上,從眾光之父那裡來的。祂不像轉動的影子變幻無常。 18祂按照自己的旨意,藉著真道重生了我們,使我們在祂所造的萬物之中好像初熟的果實。

聽道與行道

19我親愛的弟兄姊妹,請記住:每個人都要快快地聽,慢慢地說,慢慢地動怒。 20因為人的憤怒不能成就上帝的公義。 21所以你們要除去所有的污穢和一切的惡習,謙卑地領受那已經栽種在你們心裡、能救你們靈魂的真道。

22你們要行道,不要只是聽道,自己欺騙自己。 23因為人聽道而不行道,就像照鏡子一樣, 24看過後就走了,隨即忘記了自己的容貌。 25但詳細查考那使人得自由的全備律法並且持之以恆的人,不是聽了就忘,而是身體力行,這樣的人必在他所行的事上蒙福。

26如果有人自以為虔誠,卻不勒住自己的舌頭,就等於是自己欺騙自己,他的所謂虔誠也毫無價值。 27在父上帝看來,純潔無暇的虔誠是指照顧患難中的孤兒寡婦,並且不讓自己被世俗玷污。

New Amharic Standard Version

ያዕቆብ 1:1-27

1የእግዚአብሔርና የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ የሆነው ያዕቆብ፤

ለተበተኑ ለዐሥራ ሁለቱ ነገዶች፤

ሰላም ለእናንተ ይሁን።

መከራና ፈተና

2ወንድሞቼ ሆይ፤ ልዩ ልዩ መከራ ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት፤ 3ምክንያቱም የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንደሚያስገኝ ታውቃላችሁ። 4ምንም የማይጐድላችሁ ፍጹማንና ምሉኣን እንድትሆኑ ትዕግሥት ሥራውን ይፈጽም። 5ከእናንተ ማንም ጥበብ ቢጐድለው፣ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉም የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፤ ለእርሱም ይሰጠዋል። 6ዳሩ ግን ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን፤ ምክንያቱም የሚጠራጠር ሰው በነፋስ እንደሚገፋና እንደሚናወጥ የባሕር ማዕበል ነው። 7ያ ሰው፣ ከጌታ አንዳች ነገር አገኛለሁ ብሎ አያስብ፤ 8እርሱ በሁለት ሐሳብ የተያዘና በመንገዱ ሁሉ የሚወላውል ነው።

9ዝቅ ያለው ወንድም ከፍ በማለቱ ይመካ። 10ባለጠጋውም ዝቅ በማለቱ ይመካ፤ እንደ ሣር አበባ ይረግፋልና። 11ፀሓይ በነዲድ ሙቀቷ ወጥታ ሣሩን ታጠወልጋለችና፤ አበባው ይረግፋል፤ ውበቱም ይጠፋል፤ እንዲሁም ባለጠጋ ሰው፣ በዕለት ተግባሩ ሲዋትት ሳለ ይጠፋል።

12በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ምክንያቱም ፈተናን ሲቋቋም እግዚአብሔር ለሚወድዱት የሰጠውን ተስፋ፣ የሕይወትን አክሊል ያገኛል።

13ማንም ሲፈተን፣ “እግዚአብሔር ፈተነኝ” አይበል፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር በክፉ አይፈተንም፤ እርሱም ማንንም አይፈትንም፤ 14ነገር ግን እያንዳንዱ የሚፈተነው በራሱ ክፉ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ነው። 15ምኞትም ከፀነሰች በኋላ ኀጢአትን ትወልዳለች፤ ኀጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች።

16የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ አትታለሉ። 17በጎ ስጦታና ፍጹም በረከት ሁሉ ከላይ፣ ከሰማይ ብርሃናት አባት ይወርዳሉ፤ በእርሱ ዘንድ መለዋወጥ፣ ከመዞር የተነሣ የሚያርፍ ጥላም የለም። 18የፍጥረቱ በኵራት እንድንሆን በገዛ ፈቃዱ በእውነት ቃል ወለደን።

ሰምቶ በሥራ ላይ ማዋል

19የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ይህን አስተውሉ፤ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ፣ ለመናገር የዘገየ፣ ለቍጣም የዘገየ ይሁን፤ 20የሰው ቍጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አያመጣምና። 21ስለዚህ ርኩሰትንና ተንሰራፍቶ የሚገኘውን ክፋትን አስወግዳችሁ ነፍሳችሁን ማዳን የሚችለውን፣ በውስጣችሁም የተተከለውን ቃል በትሕትና ተቀበሉ።

22ቃሉ የሚናገረውን አድርጉ እንጂ ሰሚዎች ብቻ ሆናችሁ ራሳችሁን አታታልሉ። 23ቃሉን የሚሰማ፣ ነገር ግን የሚለውን የማይፈጽም ሰው ፊቱን በመስተዋት እንደሚያይ ሰው ነው፤ 24ራሱንም አይቶ ይሄዳል፤ ወዲያውም ምን እንደሚመስል ይረሳል፤ 25ነገር ግን ነጻ የሚያወጣውን ፍጹም ሕግ ተመልክቶ የሚጸና፣ የሰማውን የሚያደርግና የማይረሳ ሰው በሥራው የተባረከ ይሆናል።

26አንደበቱን ሳይገታ፣ ልቡን እያሳተ ሃይማኖተኛ ነኝ የሚል ሰው፣ ራሱን ያታልላል፤ ሃይማኖቱም ከንቱ ነው። 27በእግዚአብሔር አብ ፊት ንጹሕና ነውር የሌለበት ሃይማኖት ይህ ነው፤ ወላጆቻቸው የሞቱባቸውን ልጆችና ባሎቻቸው የሞቱባቸውን ሴቶች በችግራቸው መርዳትና ከዓለም ርኩሰት ራስን መጠበቅ ነው።