西番雅書 3 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

西番雅書 3:1-20

耶路撒冷的敗壞

1這叛逆、污穢、充滿壓迫的城有禍了!

2她不聽命令,不受管教;

不倚靠耶和華,

不親近她的上帝。

3她的首領是咆哮的獅子,

她的審判官是夜間的豺狼,

不留一點獵物到天明。

4她的先知是狂妄詭詐之徒,

她的祭司褻瀆聖殿,違背律法。

5但城中的耶和華是公義的,

祂絕不做不義之事。

祂每天早晨伸張正義,從不間斷。

然而,不義之人卻不知羞恥。

6「我已消滅列國,

摧毀他們的城樓,

使他們的街道荒廢,沒有路人;

他們的城邑淪為廢墟,杳無人跡,沒有居民。

7我以為這城一定會敬畏我,接受管教,

這樣我就不必照所定的毀滅她。

然而,他們卻更加熱衷於犯罪作惡。

8「因此,等著我吧,

等著我指控的那一天吧。

我已決定召集列國列邦,

向他們傾倒我的烈怒,

我的怒火必吞噬天下。

這是耶和華說的。

耶和華的拯救

9「那時,我必潔淨萬民的口,

以便他們可以求告我的名,

同心合意地事奉我。

10那些敬拜我的,

就是我那些分散的子民必從古實河對岸帶著供物來獻給我。

11到那天,你必不再因背叛我而感到羞愧,

因為那時我必除掉你那裡狂妄自大的人,

你在我的聖山上必不再高傲。

12我必把謙卑貧苦的人留在你那裡,

他們必投靠在我耶和華的名下。

13以色列的餘民必不再作惡,

撒謊或出詭詐之言。

他們吃喝躺臥,無人驚擾。」

歡樂之歌

14錫安3·14 」希伯來文是「女子」,可能是對錫安的暱稱。啊,歌唱吧!

以色列啊,歡呼吧!

耶路撒冷城啊,盡情地歡喜快樂吧!

15耶和華已經撤銷對你的刑罰,

趕走你的仇敵,

以色列的王耶和華與你同在,

你必不再懼怕災禍。

16到那天,耶路撒冷必聽到這樣的話:

錫安啊,不要害怕!不要雙手發軟!

17你的上帝耶和華與你同在,

祂是大能的拯救者,

祂必因你而歡喜快樂,歡然歌唱,

用祂的愛安慰你。」

18「我必招聚你那裡因不能守節期而憂愁的人,

使你不再蒙受羞辱。

19看啊,那時我必懲罰所有欺壓你的人,

拯救瘸腿的,召回分散的,

使他們的羞辱化為尊榮,聲名遠播。

20那時,我必招聚你們,帶你們回到故土。

你們回到故土後,

我必使你們在天下萬民中聲名遠播,得到尊榮。」

這是耶和華說的。

New Amharic Standard Version

ሶፎንያስ 3:1-20

የኢየሩሳሌም የወደ ፊት ዕጣ

1ለዐመፀኛዪቱና ለረከሰች፣

ለጨቋኞች ከተማ ወዮላት!

2እርሷ ለማንም አትታዘዝም፤

የማንንም ዕርምት አትቀበልም፤

በእግዚአብሔር አትታመንም፤

ወደ አምላኳም አትቀርብም።

3ሹሞቿ የሚያገሡ አንበሶች፣

ገዦቿ ለነገ የማይሉ፣

የምሽት ተኵላዎች ናቸው።

4ነቢያቷ ትዕቢተኞች፣

አታላዮችም ናቸው፤

ካህናቷ መቅደሱን ያረክሳሉ፣

በሕግም ላይ ያምፃሉ።

5በእርሷ ውስጥ ያለው እግዚአብሔር ጻድቅ ነው፤

ፈጽሞ አይሳሳትም፤

በየማለዳው ቅን ፍርድ ይሰጣል፤

በየቀኑም አይደክምም፤

ዐመፀኞች ግን ዕፍረት አያውቁም።

6“ሕዝቦችን አጥፍቻለሁ፤

ምሽጋቸው ተደምስሷል፤

ማንም እንዳያልፍባቸው፣

መንገዳቸውን ባድማ አደረግሁ፤

ከተሞቻቸው ተደምስሰዋል፤

አንድም ሰው የለም፤ ነዋሪም ከቶ አይገኝባቸውም።

7እኔም ከተማዪቱን፣

‘በርግጥ ትፈሪኛለሽ፤

ዕርምትም ትቀበያለሽ’ አልኋት፤

ስለዚህ መኖሪያዋ አይጠፋም፤

ቅጣቴም ሁሉ በእርሷ ላይ አይደርስም።

እነርሱ ግን በሚያደርጉት ሁሉ፣

ክፋትንም በመፈጸም እየተጉ ሄዱ።”

8እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለዚህ እስከምፈርድበት3፥8 የሰባ ሊቃናቱና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የዕብራይስጡ ትርጕም ግን ለመበዝበዝ እስከምነሣበት ቀን ድረስ ይላል። ቀን ድረስ

ጠብቁኝ፤

አሕዛብን ላከማች፣

መንግሥታትን ልሰበስብ፣

መዓቴንና ጽኑ ቍጣዬን

በላያቸው ላፈስስ ወስኛለሁ።

በቅናቴ ቍጣ እሳት፣

መላዋ ምድር ትቃጠላለችና።

9“በዚያ ጊዜ ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሔርን ስም እንዲጠሩ፣

ተስማምተው እንዲያገለግሉት፣

አንደበታቸውን አጠራለሁ።

10ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ፣

የሚያመልኩኝ፣ የተበተኑት ሕዝቤ

ቍርባን ያመጡልኛል።

11በእኔ ላይ ከፈጸማችሁት በደል ሁሉ የተነሣ፣

በዚያ ቀን አታፍሩም፤

በትዕቢታቸው የሚደሰቱትን፣

ከዚህች ከተማ አስወግዳለሁና፤

ከእንግዲህ ወዲያ፣

በቅዱስ ተራራዬ ላይ አትታበዩብኝም።

12በእግዚአብሔር ስም የሚታመኑትን፣

የዋሃንንና ትሑታንን፣

በመካከላችሁ አስቀራለሁ።

13የእስራኤል ቅሬታዎች ኀጢአት አይሠሩም፤

ሐሰትም አይናገሩም፤

በአንደበታቸውም ተንኰል አይገኝም።

ይበላሉ፤ ይተኛሉ፤

የሚያስፈራቸውም የለም።”

14የጽዮን ልጅ ሆይ፤ ዘምሪ፤

እስራኤል ሆይ፤ እልል በዪ፤

የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፤

በፍጹም ልብሽ ደስ ይበልሽ፤ ሐሤትም አድርጊ።

15እግዚአብሔር ቅጣትሽን አስወግዶታል፤

ጠላቶችሽን ከአንቺ መልሷል፤

የእስራኤል ንጉሥ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው፤

ከእንግዲህ ወዲያ አንዳች ክፉ ነገር አትፈሪም።

16በዚያ ቀን ኢየሩሳሌምን እንዲህ

ይሏታል፤

“ጽዮን ሆይ፤ አትፍሪ፤

እጆችሽም አይዛሉ።

17እግዚአብሔር አምላክሽ በመካከልሽ አለ፤

እርሱ ብርቱ ታዳጊ ነው፤

በአንቺ እጅግ ደስ ይለዋል፤

በፍቅሩ ያሳርፍሻል፤

በዝማሬም በአንቺ ላይ ከብሮ ደስ ይሰኛል።”

18“ስለ ክብረ በዓላት መተጓጐል የተከዝሽበትን፣

የስድብሽን ሸክም፤

ከአንቺ አስወግዳለሁ።3፥18 ወይም ስለ ክብረ በዓላት መተጓጐል የሚተክዙትን፣ የስድብ ሸክም የተከመረባቸውን መልሼ እሰበስባለሁ።

19በዚያ ጊዜ፣

ያስጨነቁሽን ሁሉ እቀጣለሁ፤

ዐንካሶችን እታደጋለሁ፤

የተበተኑትንም እሰበስባለሁ፤

በተዋረዱበት ምድር ሁሉ፣

ለውዳሴና ለክብር አደርጋቸዋለሁ።

20በዚያን ጊዜ እሰበስባችኋለሁ፤

ያን ጊዜ ወደ አገራችሁ እመልሳችኋለሁ፤

ዐይናችሁ እያየ፣

ምርኳችሁን በምመልስበት ጊዜ፣

መከበርንና መወደስን፣

በምድር ሕዝብ ሁሉ መካከል እሰጣችኋለሁ”፤

ይላል እግዚአብሔር