約珥書 3 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約珥書 3:1-21

上帝要審判萬國

1「到那日,在我復興猶大耶路撒冷的時候, 2我要聚集萬國,帶他們下到約沙法3·2 約沙法」意思是「耶和華審判」。谷,在那裡審判他們,因為他們把我的子民,就是我的產業以色列,分散到各國,並瓜分我的土地。 3他們抽籤分了我的子民,將男童換妓女,賣女童買酒喝。

4泰爾西頓非利士境內所有的人啊,你們為什麼這樣對我?你們要報復我嗎?如果你們是報復我,我必速速使你們遭報應。 5你們奪去我的金銀,搶走我的珍寶,拿去放在你們的廟中, 6並把猶大耶路撒冷的居民賣給希臘人,使他們遠離家鄉。 7然而,他們被賣到哪裡,我要從哪裡把他們帶回來,並要使你們得到報應, 8我要把你們的兒女賣給猶大人,猶大人必把他們賣給遠方的示巴人。這是耶和華說的。」

9你們去向萬國宣告:

「要召集勇士,徵調軍隊,

前去打仗!

10要將犁頭打成刀劍,

把鐮刀鑄成矛頭,

軟弱的人也要做勇士!

11四圍的列國啊,

你們快快聚集到那裡吧!」

耶和華啊,

求你差遣大能的勇士降臨。

12「萬國都要起來,

上到約沙法谷受審判,

因為我要坐在那裡審判他們。

13開鐮吧,因為莊稼熟了;

踩踏吧,因為榨酒池的葡萄滿了。

他們惡貫滿盈,如酒池滿溢。」

14千千萬萬的人聚集在審判谷,

因為耶和華的日子要臨到那裡。

15日月昏暗,

星辰無光。

16耶和華從錫安發出怒吼,

耶路撒冷發出雷聲,

天地為之震動。

但耶和華卻是祂子民的避難所,

以色列人的堡壘。

17「這樣,你們就知道我是你們的上帝耶和華,

我住在錫安——我的聖山上。

耶路撒冷必成為聖地,

外族人必不再侵犯它。

18「到那日,群山要滴下甜酒,

丘陵要流出乳汁。

猶大的溪澗碧水常流,

必有清泉從耶和華的殿中流出,

澆灌什亭谷。

19埃及必一片荒涼,

以東必成為不毛之地,

因為他們曾殘暴地對待猶大人,

猶大濫殺無辜。

20猶大必人口興盛,

耶路撒冷必存到萬代。

21我必追討3·21 追討」希伯來文是「洗淨」。尚未追討的血債,

因為耶和華住在錫安。」

New Amharic Standard Version

ኢዩኤል 3:1-21

የተፈረደባቸው ሕዝቦች

1“በዚያ ዘመን፣ በዚያ ጊዜ፣

የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ምርኮ ስመልስ፣

2አሕዛብን ሁሉ እሰበስባለሁ፤

ወደ ኢዮሣፍጥም3፥2 ኢዮሣፍጥ፣ የስሙ ትርጕም እግዚአብሔር ይፈርዳል ማለት ነው፤ 12 ላይም እንዲሁ፤ ሸለቆ አወርዳቸዋለሁ፤

ስለ ርስቴ፣ ስለ ሕዝቤ፣ ስለ እስራኤል፣

በዚያ ልፈርድባቸው እገባለሁ፤

ምድሬን ከፋፍለዋል፤

ሕዝቤንም በሕዝቦች መካከል በታትነዋልና።

3በሕዝቤ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ፤

ወንዶች ልጆችን በዝሙት ዐዳሪዎች ለወጡ፤

ወይን ጠጅ ለመጠጣትም፣

ሴቶች ልጆችን ሸጡ።

4“ጢሮስና ሲዶና እንዲሁም እናንተ የፍልስጥኤም ግዛቶች ሁሉ ሆይ፤ እንግዲህ በእኔ ላይ ምን አላችሁ? ስላደረግሁት ነገር ብድር ልትመልሱልኝ ነውን? የምትመልሱልኝ ከሆነ፣ በፍጥነትና በችኰላ እናንተ ያደረጋችሁትን በራሳችሁ ላይ መልሼ አደርግባችኋለሁ። 5ብሬንና ወርቄን ወስዳችኋል፤ የተመረጠውንም ንብረቴን ተሸክማችሁ ወደ ቤተ መቅደሳችሁ አስገብታችኋልና። 6ከገዛ ምድራቸው ልታርቋቸው፣ የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ሰዎች ለግሪኮች ሸጣችኋቸው።

7“እነሆ፤ እነርሱን ከሸጣችሁባቸው ቦታዎች አነሣሣቸዋለሁ፤ እናንተም ያደረጋችሁትን በገዛ ራሳችሁ ላይ እመልስባችኋለሁ። 8ወንዶችንና ሴቶች ልጆቻችሁን ለይሁዳ ሰዎች ሸጣለሁ፤ እነርሱም መልሰው በሩቅ ላሉት ለሳባ ሰዎች ይሸጧቸዋል፤” እግዚአብሔር ይህን ተናግሯልና።

9በሕዝቦች መካከል ይህን ዐውጁ፤

ለጦርነት ተዘጋጁ፤

ተዋጊዎችን አነሣሡ፤

ጦረኞችም ሁሉ ቀርበው ያጥቁ።

10ማረሻችሁ ሰይፍ፣

ማጭዳችሁም ጦር እንዲሆን ቀጥቅጡት፤

ደካማውም ሰው፣

“እኔ ብርቱ ነኝ” ይበል።

11እናንት በዙሪያ ያላችሁ ሕዝቦች ሁላችሁ፤

ፈጥናችሁ ኑ፤ በዚያም ተሰብሰቡ።

እግዚአብሔር ሆይ፤ ተዋጊዎችህን ወደዚያ አውርድ!

12“ሕዝቦች ይነሡ፤

ወደ ኢዮሣፍጥም ሸለቆ ፈጥነው ይውረዱ፤

ዙሪያውን ባሉት ሕዝቦች ሁሉ ላይ ልፈርድ፣

በዚያ እቀመጣለሁና።

13ማጭዱን ስደዱ፤

መከሩ ደርሷልና፤

ኑ ወይኑን ርገጡ፤

የወይን መጭመቂያው ሞልቶ፣

ከጕድጓዶቹም ተርፎ ፈስሷልና፤

ክፋታቸው እንደዚህ ታላቅ ነው።”

14ብዙ ሕዝብ፣ በጣም ብዙ ሕዝብ፣

ፍርድ በሚሰጥበት ሸለቆ ተሰብስቧል፤

ፍርድ በሚሰጥበት ሸለቆ፣

የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና።

15ፀሓይና ጨረቃ ይጨልማሉ፤

ከዋክብትም ከእንግዲህ አያበሩም።

16እግዚአብሔር ከጽዮን ጮኾ ይናገራል፤

ከኢየሩሳሌም ያንጐደጕዳል፤

ሰማይና ምድርም ይናወጣሉ፤

እግዚአብሔር ግን ለሕዝቡ መሸሸጊያ፣

ለእስራኤልም ልጆች መጠጊያ ይሆናል።

በረከት ለእግዚአብሔር ሕዝብ

17“ከዚያም እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር

በቅዱሱ ተራራዬ በጽዮን እንደምኖር ታውቃላችሁ፤

ኢየሩሳሌም የተቀደሰች ትሆናለች፤

ከእንግዲህም ወዲያ ባዕዳን አይወርሯትም።

18“በዚያ ጊዜ ተራሮች፣ አዲስ የወይን ጠጅ ያንጠባጥባሉ፤

ኰረብቶችም ወተት ያፈስሳሉ፤

በይሁዳ ያሉ ሸለቆዎች3፥18 ወይም የሸጢም ሸለቆ ሁሉ ውሃ ያጐርፋሉ፤

ከእግዚአብሔር ቤት ምንጭ ይፈልቃል፤

የሰጢምን ሸለቆ ያጠጣል።

19ግብፅ ባድማ፣

ኤዶምም ምድረ በዳ ትሆናለች፤

በምድራቸው ንጹሕ ደም በማፍሰስ፣

በይሁዳ ሕዝብ ላይ ግፍ ፈጽመዋልና።

20ይሁዳ ለዘላለም፣

ኢየሩሳሌምም ለትውልድ ሁሉ መኖሪያ ትሆናለች፤

21ደማቸውን እበቀላለሁ፤

በደለኛውንም ንጹሕ አላደርግም።”

እግዚአብሔር በጽዮን ይኖራል!