約珥書 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約珥書 1:1-20

1以下是耶和華對毗土珥的兒子約珥所說的話。

嚴重的蝗災

2長老們啊,請聽我說!

地上的所有居民啊,要留心聽!

在你們或你們祖先的時代可曾發生過這樣的事?

3要把這事告訴你們的子子孫孫,

傳到世世代代!

4蝗蟲吃剩的,蝻子來吃;

蝻子吃剩的,蚱蜢來吃;

蚱蜢吃剩的,螞蚱來吃1·4 蝗蟲蝻子蚱蜢螞蚱」四個詞希伯來語的確切意思很難考證。

5醉漢啊,醒過來哭泣吧!

貪杯的人啊,哀號吧!

你們再無美酒可飲了。

6有一群兇猛的蝗蟲侵犯我的國土,

牠們不計其數,

有雄獅的獠牙和母獅的利齒。

7牠們毀壞我的葡萄樹和無花果樹,

剝光樹皮,

只留下光禿的樹枝。

8我的子民啊,你們要像死了未婚夫的少女,

穿上喪服痛哭哀號。

9耶和華殿中的素祭1·9 素祭就是獻上五穀、麵粉之類的供物,參見利未記2章。和奠祭1·9 奠祭就是獻上新釀的酒。都停止了,

事奉耶和華的祭司都哀傷。

10田園荒廢,遍地淒涼,

五穀盡毀,

再也沒有新酒和油了。

11農夫啊,你們要憂傷!

照料葡萄園的人啊,

你們要哀號!

因為田間的大麥和小麥全毀了。

12葡萄樹枯死,

無花果樹凋殘,

石榴樹、棕樹、蘋果樹等田野的一切樹木枯乾。

人間的歡樂消逝了。

13祭司啊,穿著喪服痛哭吧;

在祭壇前事奉的人啊,要哀號;

我上帝的僕人啊,要披上麻衣過夜;

因為再無素祭和奠祭獻到你們上帝的殿中了。

14你們要定一個禁食的日子,

舉行莊嚴的聚會,

召集全國的長老和人民,

到你們的上帝耶和華的殿中,

向耶和華呼求。

15太可怕了!耶和華的日子近了,

那是全能者施行毀滅的日子。

16我們的糧食斷絕了,

我們上帝殿中的歡樂消失了。

17種子在土裡腐爛,

五穀乾死,倉庫荒廢,

穀倉被拆毀。

18牲畜哀鳴,

牛群因找不到草場而四處亂竄,

羊群也受苦。

19耶和華啊,我向你呼求,

因為火焰吞滅了曠野的草場,

烈火燒光了田野的樹木。

20田野的走獸向你呼求,

因為溪水已經枯乾,

火也燒盡了曠野的草場。

New Amharic Standard Version

ኢዩኤል 1:1-20

1ወደ ባቱኤል ልጅ ወደ ኢዩኤል የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

የአንበጣ ወረራ

2እናንት ሽማግሌዎች፣ ይህን ስሙ፤

በምድሪቱም የምትኖሩ ሁላችሁ፣ አድምጡ፤

በእናንተ ዘመንም ሆነ በአባቶቻችሁ ዘመን፣

እንዲህ ዐይነት ነገር ሆኖ ያውቃልን?

3ይህን ለልጆቻችሁ ተናገሩ፤

ልጆቻችሁ ለልጆቻቸው ይንገሩ፤

ልጆቻቸውም ለሚቀጥለው ትውልድ ይንገሩ።

4ከአንበጣ መንጋ1፥4 በዚህ ክፍል፣ ስለ አንበጦች የሚገልጹት አራት የዕብራይስጥ ቃላት፣ ትክክለኛ ትርጕም አይታወቅም። የተረፈውን፣

ትልልቁ አንበጣ በላው፤

ከትልልቁ አንበጣ የተረፈውን፣

ኵብኵባ በላው፤

ከኵብኵባ የተረፈውን፣

ሌሎች አንበጦች በሉት።

5እናንት ሰካራሞች፤ ተነሡ፤ አልቅሱ፤

እናንት የወይን ጠጅ ጠጪዎች ሁሉ፤ ዋይ በሉ፤

ስለ አዲሱ የወይን ጠጅ ዋይ ብላችሁ አልቅሱ፤

አፋችሁ ላይ እንዳለ ተነጥቃችኋልና።

6ኀያልና ቍጥር ስፍር የሌለው ሕዝብ፣

ምድሬን ወሯታልና፤

ጥርሱ እንደ አንበሳ ጥርስ፣

መንጋጋውም እንደ እንስት አንበሳ መንጋጋ ነው።

7የወይን ቦታዬን ባድማ አደረገው፤

የበለስ ዛፎቼንም ቈራረጠ፤

ቅርንጫፎቻቸው ነጭ ሆነው እስኪታዩ ድረስ፣

ቅርፊታቸውን ልጦ፣

ወዲያ ጣላቸው።

8የልጅነት ዕጮኛዋን1፥8 ወይም የልጅነት ባሏ እንዳጣች ድንግል1፥8 ወይም ወጣት ሴት

ማቅ ለብሳችሁ አልቅሱ።

9የእህል ቍርባንና የመጠጥ ቍርባን፣

ከእግዚአብሔር ቤት ተቋርጧል፤

በእግዚአብሔርም ፊት የሚያገለግሉ፣

ካህናት ያለቅሳሉ።

10ዕርሻዎች ባዷቸውን ቀርተዋል፤

ምድሩም ደርቋል1፥10 ወይም መሬቱ ያዝናል

እህሉ ጠፍቷል፤

አዲሱ የወይን ጠጅ ዐልቋል፤

ዘይቱም ተሟጧል።

11እናንት ገበሬዎች፣ ዕዘኑ፤

እናንት የወይን ገበሬዎች፣ ዋይ በሉ፤

ስለ ገብሱና ስለ ስንዴው አልቅሱ፤

የዕርሻው መከር ጠፍቷልና።

12ወይኑ ደርቋል፤

የበለስ ዛፉም ጠውልጓል፤

ሮማኑ፣ ተምሩና እንኮዩ፣

የዕርሻው ዛፎች ሁሉ ደርቀዋል፤

ስለዚህ ደስታ፣

ከሰው ልጆች ርቋል።

የንስሓ ጥሪ

13ካህናት ሆይ፤ ማቅ ለብሳችሁ አልቅሱ፤

እናንተ በመሠዊያው ፊት የምታገለግሉ፣ ዋይ በሉ፤

እናንት በአምላኬ ፊት የምታገለግሉ፣

ኑ፤ ማቅ ለብሳችሁ ዕደሩ፤

የእህል ቍርባኑና የመጠጥ ቍርባኑ፣

ከአምላካችሁ ቤት ተቋርጧልና።

14ቅዱስ ጾምን ዐውጁ፤

የተቀደሰንም ጉባኤ ጥሩ፤

ሽማግሌዎችን ሰብስቡ፤

በምድሪቱ የሚኖሩትን ሁሉ፣

ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ጥሩ፤

ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ።

15ወዮ ለዚያ ቀን፤

የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና፤

ሁሉን ከሚችል1፥15 ዕብራይስጡ ሻደይ ይለዋል። አምላክ እንደ ጥፋት ይመጣል።

16የሚበላ ምግብ፣

ከዐይናችን ፊት፣

ደስታና ተድላ፣

ከአምላካችን ቤት አልተቋረጠብንምን?

17ዘሩ በዐፈር ውስጥ1፥17 ለዚህ የገባው የዕብራይስጡ ቃል ትርጕም አይታወቅም።

በስብሶ ቀርቷል፤

ግምጃ ቤቶቹ ፈራርሰዋል፤

ጐተራዎቹም ተሰባብረዋል፤

እህሉ ደርቋልና።

18መንጎች እንደ ምን ጮኹ፣

ከብቶቹ ተደናግጠዋል፤

መሰማሪያ የላቸውምና፤

የበግ መንጎች እንኳ ተቸግረዋል።

19አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ እጣራለሁ፤

ያልተነካውን መሰማሪያ እሳት በልቶታልና፤

የዱሩን ዛፍ ሁሉ ነበልባል አቃጥሎታል።

20የዱር አራዊት እንኳ ወደ አንተ አለኸለኹ፤

ወራጁ ውሃ ደርቋል፤

ያልተነካውንም መሰማሪያ እሳት በልቶታል።