箴言 6 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

箴言 6:1-35

日常警言

1孩子啊,你若為鄰人作保,

為外人擊掌立約;

2你若被自己口中的話套住,

被自己的諾言纏住,

3孩子啊,你已落入鄰人的手中,

你當如此自救:

要謙卑地向他求情。

4勿讓你的眼睛睡覺,

莫叫你的眼皮打盹。

5要救自己脫離困境,

像羚羊掙脫獵人的手,

飛鳥逃脫捕鳥人的手。

6懶惰的人啊,去看看螞蟻,

觀察牠的生活,就會有智慧。

7螞蟻沒有元帥,

沒有官長,

也沒有君王,

8卻在夏季儲備糧食,

在收割時積聚食物。

9懶惰的人啊,你要躺到何時?

要睡到何時才起床?

10再睡一會兒,再打個盹兒,

抱著手躺一會兒,

11貧窮要像盜賊一樣攻擊你,

缺乏要像武士一樣撲向你。

12無賴與惡人滿口詭詐,

13擠眉弄眼,手腳示意,

14心術不正,設下詭計,惹事生非。

15因此,災難必突然臨到,

他們頃刻之間遭到毀滅,

無可挽救。

16耶和華所憎惡的事有六樣,

連祂厭惡的事共有七樣:

17高傲的眼睛,

撒謊的舌頭,

殺害無辜的手,

18圖謀詭計的心,

奔跑作惡的腳,

19撒謊的假證人和在弟兄中挑起爭端的人。

20孩子啊,要遵守你父親的誡命,

不可背棄你母親的訓言。

21你要常常將這些刻在心坎上,

繫在頸項上。

22你行走,它們必引領你;

你躺臥,它們必護衛你;

你醒來,它們必與你交談。

23因為誡命是燈,訓言是光,

管教責備是生命之道,

24能使你遠離邪惡的女人,

避開油嘴滑舌的妓女。

25你的心不要貪戀她的美色,

也不要被她的媚眼所迷惑,

26因為娼妓會使人傾家蕩產6·26 娼妓會使人傾家蕩產」或譯「娼妓的淫資不過是一個餅」。

淫婦會獵殺人寶貴的生命。

27人若將火藏在懷中,

哪能不燒著衣服呢?

28人若行走在火炭上,

哪能不燙傷雙腳呢?

29與別人妻子通姦也是這樣,

凡靠近她的必難逃罪責。

30賊因充饑而偷,

沒有人藐視他;

31但若被抓到,他要償還七倍,

就是傾家蕩產也要償還。

32和有夫之婦通姦的,

實在愚不可及,

他是自尋死路。

33他必挨打,受辱,

他的恥辱永難抹去。

34那丈夫妒火燃燒,

報仇時絕不留情。

35賠他再多財物,他也不會接受;

送他再多禮物,他都不肯甘休。

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 6:1-35

ከተላላነት መራቅ

1ልጄ ሆይ፤ ለጎረቤትህ ዋስ ብትሆን፣

ስለ ሌላውም ሰው እጅ መትተህ ቃል ብትገባ፣

2በተናገርኸው ነገር ብትጠመድ፣

ከአፍህ በወጣውም ቃል ብትያዝ፣

3ልጄ ሆይ፤ ራስህን ለማዳን ይህን አድርግ፤

በጎረቤትህ እጅ ስለ ወደቅህ፣

ሄደህ ራስህን አዋርድ፤

ጎረቤትህን አጥብቀህ ነዝንዘው።

4ዐይኖችህ እንቅልፍ አይያዛቸው፣

ሽፋሽፍቶችህም አያንጐላጁ።

5ከዐዳኝ እጅ እንዳመለጠች ሚዳቋ፣

ከአጥማጅ ወጥመድ እንዳፈተለከች ወፍ ራስህን አድን።

6አንተ ታካች፤ ወደ ጕንዳን ሂድ፤

ዘዴውን አስተውለህ ጠቢብ ሁን፤

7አዛዥ የለውም፤

አለቃም ሆነ ገዥ የለውም፤

8ሆኖም ግን በበጋ ምግቡን ያከማቻል፤

በመከርም ወቅት ቀለቡን ይሰበስባል።

9አንተ ታካች፤ እስከ መቼ ትተኛለህ?

ከእንቅልፍህስ መቼ ትነሣለህ?

10ጥቂት ማንቀላፋት፤ ጥቂት ማንጐላጀት፤

እጅን አጣጥፎ “እስቲ ጥቂት ልረፍ” ማለት፤

11ድኽነት እንደ ወንበዴ፣

ዕጦትም መሣሪያ እንደ ታጠቀ ሰው6፥11 ወይም እንደ ቦዘኔ ወይም ዕጦት እንደ ለማኝ ከተፍ ይልብሃል።

12ወሮበላና ጨካኝ፣

ነውረኛ አንደበቱን ይዞ የሚዞር፣

13በዐይኑ የሚጠቅስ፣

በእግሩ ምልክት የሚሰጥ፣

በጣቶቹ የሚጠቍም፣

14በልቡ ተንኰል ክፋትን የሚያውጠነጥን፣

ምንጊዜም ጠብ ይጭራል።

15ስለዚህ በቅጽበት መዓት ይወርድበታል፤

በድንገት ይጠፋል፤ መዳኛም የለውም።

16እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች አሉ፤

የሚጸየፋቸውም ሰባት ናቸው፤ እነርሱም፦

17ትዕቢተኛ ዐይን፣

ሐሰተኛ ምላስ፣

ንጹሕ ደም የሚያፈስሱ እጆች፣

18ክፋትን የሚያውጠነጥን ልብ፣

ወደ ክፋት የሚቻኰሉ እግሮች፣

19በውሸት ላይ ውሸት የሚጨምር ሐሰተኛ ምስክር፣

በወንድማማቾች መካከል ጠብን የሚጭር ሰው።

ከዝሙት መራቅ

20ልጄ ሆይ፤ የአባትህን ትእዛዝ አክብር፤

የእናትህንም ትምህርት አትተው።

21ምንጊዜም በልብህ አኑራቸው፤

በዐንገትህም ዙሪያ እሰራቸው።

22በምትሄድበት ሁሉ ይመሩሃል፤

በምትተኛበት ጊዜ ይጠብቁሃል፤

በምትነቃበት ጊዜም ያነጋግሩሃል።

23እነዚህ ትእዛዞች መብራት ናቸውና፤

ይህችም ትምህርት ብርሃን፣

የተግሣጽ ዕርምትም የሕይወት መንገድ ናት፤

24እርሷም ከምግባረ ብልሹ ሴት፣

ልዝብ አንደበት ካላት ዘልዛላ ሴት ትጠብቅሃለች።

25ውበቷን በልብህ አትመኝ፤

በዐይኗም አትጠመድ፤

26ጋለሞታ ሴት ቍራሽ እንጀራ ታሳጣሃለችና፤

አመንዝራዪቱም በሕይወትህ በራሱ ላይ ትሸምቃለች።

27ለመሆኑ ልብሱ ሳይቃጠል፣

በጕያው እሳት መያዝ የሚችል ሰው አለን?

28አንድ ሰው እግሮቹ ሳይቃጠሉ፣

በፍም ላይ መሄድ ይችላልን?

29ከሰው ሚስት ጋር የሚተኛም እንደዚሁ ነው፤

የሚደርስባትም ከቅጣት አያመልጥም።

30ሌባ በተራበ ጊዜ ራቡን ለማስታገሥ ቢሰርቅ፣

ሰዎች አይንቁትም።

31በቤቱ ያለውን ሀብት ሁሉ የሚጠይቀው ቢሆንም፣

ከተያዘ ሰባት ዕጥፍ መክፈል አለበት።

32የሚያመነዝር ሰው ግን ማመዛዘን ይጐድለዋል፤

እንዲህ የሚያደርግ ሁሉ ራሱን ያጠፋል።

33መደብደብና ውርደት ዕጣው ነው፤

ኀፍረቱም ከቶ አይወገድም፤

34ቅናት የባልን ቍጣ ይቀሰቅሳልና፤

በሚበቀልበትም ጊዜ ምሕረት አያደርግም።

35ምንም ዐይነት ካሳ አይቀበልም፤

የቱንም ያህል ብዙ ቢሆን መማለጃን እሺ አይልም።