耶利米书 15 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

耶利米书 15:1-21

犹大的厄运

1耶和华对我说:“就算摩西撒母耳站在我面前求情,我也不会怜悯这些百姓。你把他们从我面前赶走吧! 2如果他们问你,‘我们该去哪里,’你就告诉他们,耶和华这样说,

“‘该死的死,

该被杀的被杀,

该遭饥荒的遭饥荒,

该被掳的被掳。’

3“我要让他们遭受四种祸患——刀杀、狗撕、鸟啄、兽吞。这是耶和华说的。 4因为犹大希西迦的儿子玛拿西耶路撒冷的所作所为,我要使他们的遭遇令天下万国惊惧。

5耶路撒冷啊,谁会同情你?

谁会为你悲哀?

谁会驻足向你问安?

6你背弃我,远离我,

因此我要伸手攻击你,毁灭你,

不再怜悯你。

这是耶和华说的。

7我要在这片土地上的各城门口用簸箕簸散我的子民,

使他们丧掉儿女;

我要灭绝他们,

因为他们不思悔改。

8我要使他们的寡妇比海沙还多,

使毁灭者在午间突然夺取青年的性命,

以致母亲们陷入痛苦、惊恐中。

9生过七个孩子的母亲心力枯竭,奄奄一息。

她羞愧难当,

她的希望突然破灭,

犹如白昼突然变成黑夜。

我必使其余的人丧身在敌人刀下。

这是耶和华说的。”

耶利米诉苦

10母亲啊,我真不幸,因为你生了我这个跟全犹大争论、激辩的人。我没有向人借贷,也没有借贷给人,然而人人都咒骂我。 11耶和华说:“我必拯救你,我必使仇敌在灾祸、困难来临时哀求你。 12谁能折断来自北方之敌的铁拳铜臂呢? 13因为你们境内罪恶泛滥,我要使敌人任意抢掠你们的财宝, 14把你们掳到陌生的地方。我的怒火要烧灭你们。”

15耶和华啊,你知道我的遭遇。

求你顾念我,眷顾我,

报应迫害我的人。

求你不要取我的性命,

因为你不轻易发怒,

你知道我为了你忍受辱骂。

16万军之上帝耶和华啊,

我把你的话视为甘饴,

它们是我心中的快乐和喜悦,

因为我属于你的名下。

17我没有与作乐的人为伍,

没有与他们同乐。

你要我独坐一处,

他们的罪恶使我怒气填胸。

18为什么我的痛楚无休无止?

为什么我的创伤无法医治?

难道你要像一条时断时流的小溪让我无法依靠吗?

19耶和华对我说:

“如果你回心转意,

我就让你重新事奉我。

如果你说有益的话,

不说无益的话,

就可以做我的发言人,

百姓便会归向你,

但你不可受他们的影响。

20我要使你成为坚固的铜墙,

他们要攻击你,却不能胜过你,

因为我与你同在,我会保护你,

拯救你。

这是耶和华说的。

21我要把你从恶人手中救出,

从残暴之徒的权势下赎回。”

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 15:1-21

1እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “ሙሴና ሳሙኤል እንኳ በፊቴ ቢቆሙ፣ ልቤ ለዚህ ሕዝብ አይራራምና ከፊቴ አስወጣቸው፤ ይሂዱ! 2እነርሱም፣ ‘ወዴት እንሂድ?’ ቢሉህ፣ እንዲህ ብለህ ንገራቸው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ለሞት የተመደበ ወደ ሞት፣

ለሰይፍ የተመደበ ወደ ሰይፍ፣

ለራብ የተመደበ ወደ ራብ፣

ለምርኮ የተመደበ ወደ ምርኮ ይሄዳል።’

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘አራት ዐይነት አጥፊዎችን እሰድድባቸዋለሁ፤ እነዚህም፣ ለመግደል ሰይፍ፣ ለመጐተት ውሾች፣ እንዲሁም ጠራርጎ ለመብላትና ለማጥፋት የሰማይ ወፎችና የምድር አራዊት ናቸው። 4የይሁዳ ንጉሥ የሕዝቅያስ ልጅ ምናሴ በኢየሩሳሌም ካደረገው በደል የተነሣ፣ ለምድር ነገሥታት ሁሉ መሰቀቂያ አደርጋቸዋለሁ።’

5“ኢየሩሳሌም ሆይ፤ የሚራራልሽ ማን ነው?

ማንስ ያለቅስልሻል?

ደኅንነትሽንስ ማን ጐራ ብሎ ይጠይቃል?

6እኔን ጥለሽኛል” ይላል እግዚአብሔር

“ወደ ኋላም እያፈገፈግሽ ነው፤

ስለዚህ እጄን በአንቺ ላይ አነሣለሁ፤ አጠፋሻለሁም፤

ከእንግዲህም አልራራልሽም።

7በአገሪቱ የከተማ ደጆች፣

በመንሽ እበትናቸዋለሁ፤

ከመንገዳቸው አልተመለሱምና፣

ሕዝቤን በሐዘን እመታለሁ፤

ጥፋትም አመጣባቸዋለሁ፤

8የመበለቶቻቸውን ቍጥር፣

ከባሕር አሸዋ ይልቅ አበዛለሁ፤

የጐበዛዝት እናቶች በሆኑትም ላይ፣

አጥፊውን በቀትር አመጣባቸዋለሁ።

ሽብርንና ድንጋጤን፣

በድንገት አወርድባቸዋለሁ።

9የሰባቶቹ እናት ትዝለፈለፋለች፤

ትንፋሿም ይጠፋል፤

ገና ቀን ሳለ ፀሓይዋ ትጠልቃለች፤

እርሷም ታፍራለች፤ ትዋረዳለችም፤

የተረፉትንም በጠላቶቻቸው ፊት፣

ለሰይፍ እዳርጋቸዋለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

10ወይኔ እናቴ! ለምድር ሁሉ፣

የጭቅጭቅና የክርክር ሰው የሆንሁትን ምነው ወለድሽ!

ለማንም አላበደርሁም፤ ከማንም አልተበደርሁም፤

ነገር ግን ሰው ሁሉ ይረግመኛል።

11እግዚአብሔር እንዲህ አለ፤

“በርግጥ ለበጎ ዐላማ እታደግሃለሁ፤

በመከራና በጭንቅ ጊዜም፣

ጠላቶችህ ደጅ እንዲጠኑህ በእውነት አደርጋለሁ።

12“ሰው ብረትን፣ ከሰሜን የመጣን ብረት፣

ነሐስንስ መስበር ይችላልን?

13በመላ አገርህ፣

ስላለው ኀጢአትህ ሁሉ፣

ሀብትና ንብረትህን፣

ያለ ዋጋ አሳልፌ ለምርኮ እሰጣለሁ።

14ቍጣዬ በላያችሁ፣

የሚነድድ እሳት ትጭራለችና፣

በማታውቀው አገር፣

ለጠላቶችህ15፥14 አንዳንድ የዕብራይስጥ ጽሑፎች፣ ሰብዓ ሊቃናትና ሱርሰት ጽሑፎች ጠላቶችህ እንዲወስዱህ አደርጋለሁ ይላሉ። ባሪያ አደርግሃለሁ።”

15እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ታውቃለህ፤

እንግዲህ አስበኝ፤ ጐብኘኝም፤

አሳዳጆቼን ተበቀልልኝ።

ታጋሽ እንደ መሆንህ አታጥፋኝ፤

ባንተ ምክንያት የሚደርስብኝን ነቀፋ ዐስብ።

16ቃልህ በተገኘ ጊዜ በላሁት፤

የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤

በስምህ ተጠርቻለሁና፣

ቃልህ ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነልኝ።

17ፈንጠዝያ ከሚያደርጉት ጋር አልተቀመጥሁም፤

ከእነርሱም ጋር አልፈነጨሁም፤

እጅህ በላዬ ስለ ነበር፣ በቍጣህ ስለ ሞላኸኝ፣

ለብቻዬ ተቀመጥሁ።

18ሕመሜ ለምን ጸናብኝ?

ቍስሌስ ለምን በረታብኝ? ለምንስ የማይፈወስ ሆነ?

እንደሚያታልል ወንዝ፣

እንደሚያሳስት ምንጭ ትሆንብኛለህን?

19ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ብትመለስ፣ መልሼ አቆምሃለሁ፤

ታገለግለኛለህም፤

የከበረውን ከማይረባው ለይተህ ብትናገር፣

አፍ ትሆነኛለህ፤

እነርሱ ወደ አንተ ይመለሳሉ እንጂ፣

አንተ ወደ እነርሱ አትመለስም፤

20ለዚህ ሕዝብ የናስ ቅጥር፣ የተመሸገ

የናስ ቅጥር አደርግሃለሁ፤

ልታደግህና፣ ላድንህም፣

እኔ ከአንተ ጋር ነኝና፤

ቢዋጉህም እንኳ፣

ሊያሸንፉህ አይችሉም፤”

ይላል እግዚአብሔር

21“ከክፉዎች እጅ እቤዥሃለሁ፤

ከጨካኞችም ጭምደዳ እታደግሃለሁ።”