彼得前书 3 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

彼得前书 3:1-22

夫妻之道

1-2照样,做妻子的要顺服丈夫。这样,即使丈夫不信从真道,也会因为看见妻子贞洁和敬虔的品行而被无声地感化。 3你们不要注重外表的妆饰,像编头发、戴金饰或穿华丽的衣服, 4要以温柔、娴静这些永不褪色的内在美为妆饰,这是上帝所看重的。 5从前那些仰赖上帝的圣洁妇女,都是以这些来妆饰自己,并顺服自己的丈夫, 6正如撒拉顺服亚伯拉罕,称他为主人。所以,如果你们做对的事,不怕恐吓,就是撒拉的女儿。

7你们做丈夫的也一样,要按情理3:7 按情理”希腊文是“按知识”。与妻子共同生活,因为她们比你们软弱。要敬重她们,因为她们和你们一同承受上帝施恩赐下的生命。这样,你们的祷告就可以畅通无阻了。

要为义受苦

8总而言之,你们要同心合意,互相关怀,彼此相爱,仁慈谦虚。 9不要以恶报恶,以辱骂还辱骂,反要祝福对方,这是你们蒙召的目的,好叫你们得到祝福。 10因为圣经上说:

“若有人热爱生命,

渴望幸福,

就要舌头不出恶言,

嘴唇不说诡诈的话。

11要弃恶行善,竭力追求和睦。

12因为主的眼睛看顾义人,

祂的耳朵垂听他们的祈求。

但主必严惩作恶之人。”

13如果你们热心行善,有谁会害你们呢? 14就算你们为义受苦,也是有福的。不要害怕别人的恐吓3:14 不要害怕别人的恐吓”或译“不要怕别人所怕的”。,也不要惊慌, 15要心里尊基督为主。如果有人问起你们心中的盼望,你们要随时准备答复, 16但态度要温和恭敬,存无愧的良心。这样,那些对你们因信基督而有的好品行妄加诬蔑的人会自觉羞愧。 17如果上帝的旨意是要你们因行善而受苦,这也总比你们因作恶而受苦强。

18因为基督也曾一次为罪受苦,以无罪之身代替不义之人,为要领你们到上帝面前。祂的肉体虽被处死,但祂借着圣灵复活了。 19祂还借着圣灵向那些监狱中的灵魂传道, 20他们就是从前在挪亚造方舟、上帝耐心等候人们悔改的时代中那些不肯信的人。当时进入方舟,从洪水中得救的人很少,只有八个人。 21这水代表的洗礼现在借着耶稣基督的复活也拯救了你们。这洗礼要表明的不是除掉肉体的污秽,而是求在上帝面前有无愧的良心。 22基督已经升到天上,坐在上帝的右边,众天使、掌权的、有能力的都服从了祂。

New Amharic Standard Version

1 ጴጥሮስ 3:1-22

በባልና በሚስት መካከል ሊኖር የሚገባ ግንኙነት

1ሚስቶች ሆይ፤ እናንተም እንደዚሁ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤ አንዳንድ ለቃሉ የማይታዘዙ ቢኖሩ፣ ያለ ቃል በሚስቶቻቸው አኗኗር ተማርከው ይመለሳሉ፤ 2ይህም የሚሆነው ንጹሕና ፍጹም አክብሮት የተሞላውን ኑሯችሁን ሲመለከቱ ነው። 3ውበታችሁ በውጫዊ ነገሮች በመሽሞንሞን፣ ይኸውም፣ ሹሩባ በመሠራት፣ በወርቅ በማጌጥና በልብስ አይሁን፤ 4ነገር ግን ውበታችሁ በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ፣ ገርና ጭምት መንፈስ ያለበት፣ ምንጊዜም የማይጠፋ የውስጥ ሰውነት ውበት ይሁን፤ 5ተስፋቸውን በእግዚአብሔር ላይ የጣሉ የቀድሞ ቅዱሳን ሴቶች ራሳቸውን ያስዋቡት በዚህ ዐይነት ለባሎቻቸው በመገዛት ነበርና። 6ሣራም አብርሃምን “ጌታዬ” እያለች ትታዘዘው ነበር፣ እናንተም ምንም ሳትፈሩ መልካም ብታደርጉ የእርሷ ልጆች ናችሁ።

7ባሎች ሆይ፤ እናንተም ደግሞ ጸሎታችሁ እንዳይደናቀፍ በኑሯችሁ ሁሉ ለሚስቶቻችሁ ዐስቡላቸው፤ ደካሞች ስለሆኑና የሕይወትንም በረከት አብረዋችሁ ስለሚወርሱ አክብሯቸው።

መልካም በማድረግ መከራን መቀበል

8በመጨረሻም ሁላችሁ በአንድ ሐሳብ ተስማሙ፤ እርስ በርሳችሁ ተሳሰቡ፤ እንደ ወንድማማቾች ተዋደዱ፤ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ። 9ክፉን በክፉ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ፤ በዚህ ፈንታ ባርኩ፤ ምክንያቱም እናንተ የተጠራችሁት እንደነዚህ ያሉትን ነገሮች እያደረጋችሁ በረከትን ለመውረስ ነው። 10ስለዚህ፣

“ሕይወትን የሚወድድ፣

መልካም ቀኖችን ሊያይ የሚፈልግ፣

ምላሱን ከክፉ፣

ከንፈሮቹንም ተንኰል ከመናገር ይከልክል።

11ከክፉ ይራቅ፤ መልካምንም ያድርግ፤

ሰላምን ይፈልግ፤ ይከተላትም፤

12ምክንያቱም የጌታ ዐይኖች ጻድቃንን ይመለከታሉና፤

ጆሮቹም ጸሎታቸውን ለመስማት የተከፈቱ ናቸው፤

የጌታ ፊት ግን በክፉ አድራጊዎች ላይ ነው።”

13መልካም ነገር ለማድረግ ብትቀኑ የሚጐዳችሁ ማን ነው? 14ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራ ቢደርስባችሁ ብፁዓን ናችሁ፤ “ዛቻቸውን አትፍሩ3፥14 ወይም የሚፈሩትን አትፍሩ፤ አትታወኩም።” 15ክርስቶስን ጌታ አድርጋችሁ በልባችሁ ቀድሱት። እናንተ ስላላችሁ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ሁልጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ፤ ነገር ግን ይህን ሁሉ በትሕትናና በአክብሮት አድርጉት፤ 16በክርስቶስ ያላችሁን መልካም ጠባይ አክፋፍተው የሚናገሩ ሰዎች በሐሜታቸው እንዲያፍሩ በጎ ኅሊና ይኑራችሁ። 17የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲህ ከሆነ፣ ክፉ ሠርቶ መከራ ከመቀበል ይልቅ መልካም አድርጎ መከራ መቀበል ይሻላል፤ 18እንዲሁም ክርስቶስ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ስለ ኀጢአት ሞቷልና፤ ወደ እግዚአብሔር ያቀርባችሁ ዘንድ ጻድቅ የሆነው እርሱ ስለ ዐመፀኞች ሞተ፤ እርሱ በሥጋ ሞተ፤ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ፤ 19በመንፈስም ሄዶ በወህኒ ቤት ለነበሩ ነፍሳት ሰበከላቸው። 20እነዚህ በወህኒ የነበሩት ነፍሳት ቀድሞ በኖኅ ዘመን መርከብ ሲሠራ እግዚአብሔር በትዕግሥት ይጠብቃቸው የነበሩ እንቢተኞች ናቸው፤ በውሃ የዳኑት ጥቂት፣ ይኸውም ስምንት ሰዎች ብቻ ነበሩ። 21ይህም ውሃ አሁን የጥምቀት ምሳሌ ሆኖ ያድናችኋል፤ ይህም የሰውነትን እድፍ በማስወገድ ሳይሆን በንጹሕ ኅሊና በእግዚአብሔር ፊት የሚቀርብ መማፀኛ3፥21 ወይም ምላሽ ነው፤ የሚያድናችሁም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አማካይነት ነው፤ 22እርሱም ወደ ሰማይ ወጥቶ በእግዚአብሔር ቀኝ አለ፤ መላእክትና ሥልጣናት፣ ኀይላትም ተገዝተውለታል።