哥林多前书 3 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

哥林多前书 3:1-23

同是上帝的仆人

1弟兄姊妹,以前我对你们讲话的时候,还不能把你们看作属灵的人,只能把你们看作属肉体的人,是在基督里的婴孩。 2我只能用奶而不能用饭来喂养你们,因为你们当时不能消化,甚至现在也不能。 3你们仍然是属肉体的人,因为你们中间有嫉妒、争斗。这岂不证明你们是属肉体的,行事为人和世人一样吗? 4你们有的说:“我是跟随保罗的”,有的说:“我是跟随亚波罗的”,这岂不证明你们和世人一样吗?

5亚波罗算什么?保罗算什么?我们不过是上帝的仆人,各人照着主所赐的才干引导你们信靠上帝。 6我栽种,亚波罗灌溉,但使之生长的是上帝。 7所以栽种的和灌溉的都算不得什么,一切都在于使之生长的上帝。 8其实栽种的人和浇灌的人目标都一样,各人将按照自己的付出得报酬。 9因为我们是上帝的同工,你们是上帝的园地和建筑。

10我照着上帝赐给我的恩典,好像一位有智慧的建筑师打稳了根基,然后让其他的工人在上面建造。但每个人建造的时候要小心, 11因为除了那已经奠定的根基——耶稣基督以外,没有人能另立根基。 12人们用金、银、宝石、草、木或禾秸在这根基上建造, 13每个人的工程将来都会显明出来,因为到了审判的日子,必用火试验各人工程的品质。 14人在这根基上所建造的工程若经得起考验,他必获得奖赏。 15人的工程若被烧毁了,他必遭受损失,自己虽然可以得救,却像火里逃生一样。

16岂不知你们就是上帝的殿,上帝的灵住在你们里面吗? 17若有人摧毁上帝的殿,上帝必摧毁那人,因为上帝的殿是神圣的,你们就是这殿。

18你们不要自欺。如果你们有人自以为在世上有智慧,他应当变成愚人,好成为真正的智者。 19因为这世上的智慧在上帝的眼中都是愚昧的,正如圣经上说:“上帝使智者中了自己的诡计。” 20又说:“主知道智者的思想虚妄。” 21因此,谁都不要仗着人夸耀,因为万物都属于你们, 22无论是保罗亚波罗彼得、世界、生命、死亡、现在的事或将来的事都属于你们, 23你们属于基督,基督属于上帝。

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 3:1-23

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተከሠተ መለያየት

1ወንድሞች ሆይ፤ በክርስቶስ ገና ሕፃናት እንደ መሆናችሁ፣ እንደ ሥጋውያን እንጂ እንደ መንፈሳውያን ልናገራችሁ አልቻልሁም። 2ገና ስላልጠነከራችሁ ወተት እንጂ ጠንካራ ምግብ አልመገብኋችሁም፤ አሁንም ቢሆን ገና ናችሁ። 3አሁንም ሥጋውያን ናችሁ፤ በመካከላችሁ ቅናትና ክርክር አለ። ታዲያ፣ ሥጋውያን መሆናችሁ አይደለምን? ተግባራችሁስ እንደ ማንኛውም ሰው ተግባር መሆኑ አይደለምን? 4ምክንያቱም አንዱ፣ “እኔ የጳውሎስ ነኝ”፣ ሌላው ደግሞ፣ “እኔ የአጵሎስ ነኝ” ቢል፣ ሰብአዊ ፍጡር ብቻ መሆናችሁ አይደለምን?

5ለመሆኑ አጵሎስ ምንድን ነው? ጳውሎስስ ምንድን ነው? ጌታ ለእያንዳንዳቸው በሰጣቸው መጠን የሚሠሩ አገልጋዮች ናቸው፤ እናንተም ወደ እምነት የመጣችሁት በእነርሱ አማካይነት ነው። 6እኔ ተከልሁ፤ አጵሎስ ውሃ አጠጣ፤ ያሳደገው ግን እግዚአብሔር ነው። 7ስለዚህ የሚያሳድግ እግዚአብሔር እንጂ፣ የሚተክልም ሆነ ውሃ የሚያጠጣ ምንም አይደለም። 8የሚተክልም ሆነ የሚያጠጣ አንድ ናቸው፤ እያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን የራሱን ሽልማት ይቀበላል። 9እኛ ከእግዚአብሔር ጋር አብረን የምንሠራ ነንና፤ እናንተም የእግዚአብሔር ዕርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንጻ ናችሁ።

10ከእግዚአብሔር በተሰጠኝ ጸጋ መጠን፣ እንደ አንድ ብልኅ ግንበኛ መሠረትን ጣልሁ፤ ሌላውም በላዩ ላይ ይገነባል፤ ነገር ግን እያንዳንዱ እንዴት እንደሚገነባ መጠንቀቅ አለበት። 11ምክንያቱም አንድ ጊዜ ከተመሠረተው መሠረት በቀር ሌላ መሠረት መጣል የሚችል ማንም የለም፤ ይህም መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። 12ማንም በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ወይም በብር፣ በከበረ ድንጋይ ወይም በዕንጨት፣ በሣር ወይም በአገዳ ቢያንጽ፣ 13ሥራው እንዴት እንደ ሆነ ይታያል፤ ምክንያቱም ያ ቀን ወደ ብርሃን ያመጣዋል። በእሳት ስለሚገለጥ እሳቱ የእያንዳንዱን ሰው ሥራ ምንነት ይፈትናል።

14ማንም የገነባው ሥራ ቢጸናለት ሽልማቱን ይቀበላል፤ 15ሥራው የተቃጠለበት ግን ሽልማት ይቀርበታል፤ እርሱ ራሱ ግን ይድናል፤ ይሁን እንጂ የሚድነው በእሳት ውስጥ በጭንቅ እንደሚያልፍ ሆኖ ነው።

16እናንተ ራሳችሁ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ፣ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውስጣችሁ እንደሚኖር አታውቁምን? 17ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፤ ያም ቤተ መቅደስ እናንተ ናችሁ።

18ማንም ራሱን አያታልል፤ ከእናንተ ማንም በዚህ ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው፣ ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ራሱን እንደ ሞኝ ይቍጠር። 19የዚህ ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና፤ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና፤ “እርሱ ጥበበኞችን በራሳቸው ተንኰል ይይዛቸዋል፤” 20በሌላ ስፍራ ደግሞ፣ “ጌታ የጥበበኞች ሐሳብ ከንቱ መሆኑን ያውቃል” ተብሎ ተጽፏል፤ 21እንግዲህ ማንም በሰው አይመካ። ሁሉ ነገር የእናንተ ነውና፤ 22ጳውሎስም ሆነ አጵሎስ ወይም ኬፋ3፥22 ጴጥሮስ ማለት ነው።፣ ዓለምም ሆነ ሕይወት ወይም ሞት፣ አሁን ያለውም ሆነ ወደ ፊት የሚመጣው፣ ሁሉ የእናንተ ነው፤ 23እናንተም የክርስቶስ ናችሁ፤ ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው።