利未记 11 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

利未记 11:1-47

有关食物的条例

1耶和华对摩西亚伦说: 2“你们把以下条例告诉以色列人。

“地上的动物, 3凡是蹄子分瓣且反刍的,你们都可以吃。 4但你们不可吃只有蹄子分瓣或只反刍的动物。骆驼不洁净,因为它虽反刍但蹄子不分瓣; 5獾不洁净,因为它虽反刍但蹄子不分瓣; 6野兔不洁净,因为它虽反刍但蹄子不分瓣; 7猪不洁净,因为它蹄子虽分瓣但不反刍。 8你们不可吃它们的肉,也不可摸它们的尸体,因为它们对你们来说不洁净。

9“海洋与河流里的动物,凡有鳍有鳞的,你们都可以吃。 10但海洋与河流里无鳍无鳞的动物,你们要憎恶。 11它们都是可憎之物,不可吃它们的肉,也不可摸它们的尸体。 12水中任何无鳍无鳞的动物,你们都要视为可憎之物。

13“你们不可吃以下鸟类,要视为可憎之物。它们是雕、胡兀鹫、黑秃鹫、 14鸢、隼类、 15乌鸦类、 16驼鸟、夜鹰、海鸥、鹰类、 17小鸮、鸬鹚、大鸮、 18仓鸮、鹈鹕、鱼鹰、 19鹳、鹭鸟类、戴胜和蝙蝠。

20“你们要憎恶会飞会爬的昆虫, 21但可以吃会飞会跳的昆虫, 22包括蝗虫、蟋蟀和蚱蜢。 23所有会飞会爬的昆虫,你们要视为可憎之物。

24“以下的动物会使你们不洁净。任何人接触到它们的尸体,都不洁净,要等到傍晚才能洁净。 25任何人拿它们的尸体,都必须洗净所穿的衣服,要等到傍晚才能洁净。 26蹄子不分瓣或不反刍的动物,你们要视为不洁净,碰到它们的人都不洁净。 27所有以脚掌走路的四足动物,你们要视为不洁净,碰到它们尸体的人都不洁净,要等到傍晚才能洁净。 28凡拿它们尸体的人都必须洗净所穿的衣服,要等到傍晚才能洁净。你们要视它们为不洁净的动物。

29“地上不洁净的动物有鼬鼠、老鼠、大蜥蜴、 30壁虎、巨蜥、小蜥蜴和变色龙。 31这些爬虫都是不洁净的。任何人碰到它们的尸体,都不洁净,要等到傍晚才能洁净。 32如果它们的尸体掉在什么东西上,不管是木器、衣物、皮件还是袋子,不管作何用途,都会变得不洁净。要把那东西放在水中,一直到傍晚才能洁净。 33如果它们的尸体掉在陶器里,陶器里盛的东西都不洁净。你们必须打碎那陶器。 34陶器里的水如果滴到食物上,食物就不洁净;如果滴到盛饮料的器皿里,饮料也不洁净。 35它们的尸体无论掉在什么东西上,那东西都不洁净,无论是炉是锅都要打碎。 36如果它们的尸体掉进水泉或储水池里,水泉和储水池仍然是洁净的,但碰到尸体的人是不洁净的。 37如果它们的尸体接触到将要播撒的种子,种子仍是洁净的。 38但如果它们的尸体碰到泡过水的种子,种子就不洁净。

39“一只可以食用的动物死后,任何人如果碰到它的尸体,都不洁净,要等到傍晚才能洁净。 40任何人如果吃它的肉,或拿它的尸体,都必须洗净衣服,等到傍晚才能洁净。

41“所有地上的爬虫都是可憎的,你们不可吃。 42你们不可吃用肚子、四脚或多脚爬行的动物,这些都是可憎的。 43你们不可让这些动物玷污自己,使自己不洁净。 44我是你们的上帝耶和华。你们要分别出来做圣洁的人,因为我是圣洁的。你们不可让地上的爬虫玷污自己。 45我是耶和华,我带你们离开埃及,为要做你们的上帝。你们要圣洁,因为我是圣洁的。

46“以上是有关飞禽走兽、水族和地上一切爬虫的条例, 47使你们可以分清什么是洁净的、什么是不洁净的、什么是可吃的、什么是不可吃的。”

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 11:1-47

የተፈቀደና ያልተፈቀደ መብል

11፥1-23 ተጓ ምብ – ዘዳ 14፥3-20

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“እስራኤላውያንን እንዲህ በሏቸው፤ ‘በየብስ ከሚኖሩ እንስሳት ሁሉ የምትበሏቸው እነዚህ ናቸው፦ 3ሰኰናው የተሰነጠቀውን የሚያመሰኳውን ማንኛውንም እንስሳ መብላት ትችላላችሁ።

4“ ‘የሚያመሰኩ ሆነው ሰኰናቸው ያልተሰነጠቀ ወይም ሰኰናቸው የተሰነጠቀ ሆኖ የማያመሰኩትን አትብሉ፤ ግመል ያመሰኳል፤ ሰኰናው ስላልተሰነጠቀ ግን በእናንተ ዘንድ ርኩስ ይሁን። 5ሽኮኮ ያመሰኳል፤ ሰኰናው ስላልተሰነጠቀ ግን በእናንተ ዘንድ ርኩስ ይሁን። 6ጥንቸል ያመሰኳል፤ ሰኰናው ስላልተሰነጠቀ ግን በእናንተ ዘንድ ርኩስ ይሁን። 7ዐሳማ ሰኰናው የተሰነጠቀ ቢሆንም ስለማያመሰኳ በእናንተ ዘንድ ርኩስ ይሁን። 8የእነዚህን እንስሳት ሥጋ አትብሉ፤ ጥንባቸውንም አትንኩ፤ በእናንተ ዘንድ ርኩሶች ይሁኑ።

9“ ‘በባሕሮችና በወንዞች ውሃ ውስጥ ከሚኖሩት ፍጡሮች ክንፍና ቅርፊት ያላቸውን መብላት ትችላላችሁ፤ 10ነገር ግን በባሕሮችና በወንዞች ውስጥ ከሚኖሩት ፍጡሮች ሁሉ፣ ከሚንፏቀቁት ወይም በውሃ ውስጥ ከሚኖሩት ሕይወት ካላቸው ሌሎች ፍጡሮች መካከል ክንፍና ቅርፊት የሌላቸው በእናንተ ዘንድ አስጸያፊዎች ይሁኑ፤ 11በእናንተ ዘንድ አስጸያፊ ስለ ሆኑ ሥጋቸውን አትብሉ፤ በድናቸውንም ትጸየፋላችሁ፤ 12ክንፍና ቅርፊት የሌለው ማንኛውም በውሃ ውስጥ የሚኖር ፍጡር በእናንተ ዘንድ አስጸያፊ ይሁን።

13“ ‘ከአዕዋፍ ወገን እነዚህን ትጸየፋላችሁ፤ ጸያፍ ስለ ሆኑም አትብሏቸው፦ ንስር፣ ጥንብ አንሣ፣ ግልገል አንሣ፣ 14ጭላት፣ ማንኛውም ዐይነት ጭልፊት፣ 15ማንኛውም ዐይነት ቍራ፣ 16ሰጐን፣ ጠላቋ፣ ዝይ፣ ማንኛውም ዐይነት በቋል፣ 17ጕጕት፣ ርኩም፣ ጋጋኖ፣ 18የውሃ ዶሮ፣ ይብራ፣ ስደተኛ አሞራ፣ 19ሽመላ፣ ማንኛውም ዐይነት ሳቢሳ፣ ጅንጁላቴ ወፍና የሌሊት ወፍ።11፥19 በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ያሉ የእያንዳንዱ አዕዋፍ፣ ነፍሳትና እንስሳት ትክክለኛ ማንነታቸው በትክክል አይታወቅም

20“ ‘ክንፍ ኖሯቸው በአራት እግር የሚንቀሳቀሱ ነፍሳት ሁሉ በእናንተ ዘንድ አስጸያፊዎች ይሁኑ። 21ነገር ግን ክንፍ ኖሯቸው በአራት እግር ከሚንቀሳቀሱ ነፍሳት መካከል ከምድር በሚፈናጠሩበት እግራቸው አንጓ ያለባቸውን መብላት ትችላላችሁ። 22ከእነዚህ ማንኛውንም ዐይነት አንበጣ፣ ፌንጣና ኵብኵባ መብላት ትችላላችሁ። 23ነገር ግን ክንፍ ኖሯቸው በአራት እግር የሚንቀሳቀሱትን ፍጥረታት ተጸየፏቸው።

24“ ‘ከእነዚህ የተነሣ ትረክሳላችሁ፤ የእነዚህን በድን የሚነካ ሁሉ እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል። 25የእነዚህንም በድን የሚያነሣ ሰው ሁሉ ልብሱን ይጠብ፤ ሆኖም እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ነው።

26“ ‘ሰኰና ያለው፣ ነገር ግን ሰኰናው ያልተሰነጠቀና የማያመሰኳ ማንኛውም እንስሳ በእናንተ ዘንድ ርኩስ ይሁን። የእነዚህንም በድን የሚነካ ሰው ሁሉ ይረክሳል። 27አራት እግር ካላቸው እንስሳት ሁሉ በመዳፋቸው የሚሄዱት በእናንተ ዘንድ ርኩሳን ናቸው፤ በድናቸውንም የሚነካ ሁሉ እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል። 28የእነዚህን በድን የሚያነሣ ሰው ልብሱን ይጠብ፤ ሆኖም እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል፤ እንስሳቱም በእናንተ ዘንድ ርኩሳን ናቸው።

29“ ‘ምድር ለምድር ከሚንቀሳቀሱ እንስሳት መካከል እነዚህ በእናንተ ዘንድ ርኩሳን ናቸው፦ ሙጭልጭላ፣ ዐይጥ፣ እንሽላሊት በየወገኑ፣ 30ዔሊ፣ ዐዞ፣ ገበሎ፣ አርጃኖ፣ ዕሥሥት። 31ምድር ለምድር ከሚንቀሳቀሱ እንስሳት ሁሉ መካከል እነዚህ በእናንተ ዘንድ ርኩሳን ናቸው፤ ከእነዚህም የሞተውን የሚነካ ሁሉ እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል። 32በድኑ በማንኛውም ዕቃ ላይ ቢወድቅ ያ ዕቃ ከዕንጨት፣ ከጨርቅ፣ ከቈዳ ወይም ከበርኖስ የተሠራ ቢሆን ርኩስ ይሆናል፤ በውሃ ውስጥ ይደረግ፤ ሆኖም ርኩስ ነው፤ ከዚያም በኋላ ንጹሕ ይሆናል። 33በድኑም በሸክላ ዕቃ ውስጥ ቢወድቅ፣ በውስጡ ያለ ነገር ሁሉ ርኩስ ስለሚሆን ዕቃውን ስበሩት። 34ማንኛውም ምግብ እንዲህ ካለው ዕቃ ውሃ ቢፈስስበት ይረክሳል፤ ከዚህ ዕቃ የሚጠጣውም ነገር ሁሉ ርኩስ ነው። 35ከበድናቸው አንዱ የወደቀበት ነገር ሁሉ ይረክሳል፤ ምድጃም ይሁን ማሰሮ ይሰበር፤ ርኩሳን ናቸው፤ እናንተም ተጸየፏቸው። 36ነገር ግን ምንጭ ወይም የውሃ ማጠራቀሚያ ጕድጓድ ንጹሕ እንደ ሆነ ይቈያል፤ ሆኖም በድኑን የነካ ይረክሳል። 37በሚዘራ ዘር ላይ በድን ቢወድቅ ዘሩ ንጹሕ እንደ ሆነ ይቈያል። 38ነገር ግን በዘሩ ላይ ውሃ ከፈሰሰበት በኋላ በድን ቢወድቅበት ዘሩ በእናንተ ዘንድ ርኩስ ነው።

39“ ‘እንድትበሉ ከተፈቀደላችሁ እንስሳት አንዱ ቢሞት፣ በድኑን የሚነካ ማንኛውም ሰው እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል። 40ማንም ሰው ከበድኑ ቢበላ ልብሱን ይጠብ፤ ሆኖም እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ነው፤ በድኑን የሚያነሣ ልብሱን ይጠብ፤ ሆኖም እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል።

41“ ‘ምድር ለምድር የሚንቀሳቀስ ማንኛውም ፍጡር ጸያፍ ነው፤ አይበላም። 42ምድር ለምድር የሚንቀሳቀሰውን ፍጡር ሁሉ፣ ይኸውም በደረቱ የሚሳበውን ወይም በአራት እግር የሚሄደውን ወይም ብዙ እግሮች ያሉትን አትብሉ፤ ጸያፍ ነው። 43በእነዚህ ፍጡራን ሁሉ ራሳችሁን አስጸያፊ አታድርጉ፤ በእነርሱም ራሳችሁን በማጕደፍ አትርከሱ። 44እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ቅዱስ ነኝና እናንተም ተለዩ፤ ቅዱሳንም ሁኑ፤ ምድር ለምድር በሚንቀሳቀስ በማንኛውም ፍጡር ራሳችሁን አታርክሱ። 45አምላካችሁ (ኤሎሂም) እሆን ዘንድ ከግብፅ ምድር ያወጣኋችሁ እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነኝ፤ ስለዚህ እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ።

46“ ‘እንስሳትንና አዕዋፍን፣ በውሃ ውስጥ የሚኖሩትንና ምድር ለምድር የሚንቀሳቀሱትን ፍጥረታት ሁሉ በሚመለከት የተሰጠ ሕግ ይህ ነው። 47በዚህም በርኩሱና በንጹሑ መካከል፣ እንዲሁም ሕይወት ካላቸው ፍጡራን የሚበሉትንና የማይበሉትን ትለያላችሁ።’ ”