出埃及记 6 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

出埃及记 6:1-30

上帝应许拯救以色列人

1耶和华对摩西说:“你就要看见我怎样用大能的手对付法老,那时他会让以色列人走,甚至把他们赶出埃及!” 2上帝又对摩西说:“我是耶和华, 3我曾以全能上帝的身份向亚伯拉罕以撒雅各显现,但没有让他们知道我的名字是耶和华。 4我向他们坚守所立的约,要把他们寄居的迦南赐给他们。 5我已听见以色列人因受埃及人的奴役而发出的呼求,也想起了我的约。 6所以,你要转告以色列人说,‘我是耶和华。我要伸出臂膀重重地惩罚埃及,救赎你们脱离埃及人的辖制,脱离他们的奴役。 7我要接纳你们做我的子民,我要做你们的上帝。这样,你们就知道我是你们的上帝耶和华,曾救你们脱离埃及人的辖制。 8我必带领你们进入我举手起誓要给亚伯拉罕以撒雅各的那片土地,把它赐给你们作产业。我是耶和华。’”

9摩西把这番话转告百姓,可是他们因为残酷的劳役无比沮丧,不肯听他的话。 10耶和华对摩西说: 11“你再去见法老,要他让以色列人离开他的土地。” 12摩西却说:“以色列人都不听我的话,法老又怎么肯听我这拙口笨舌的人呢?” 13耶和华吩咐摩西亚伦回到以色列人和法老那里,要他们领以色列人离开埃及

摩西和亚伦的族谱

14以下是以色列各宗族族长的名字:

以色列长子吕便的儿子是哈诺法路希斯仑迦米。这些是吕便的宗族。

15西缅的儿子是耶姆利雅悯阿辖雅斤琐辖扫罗扫罗的母亲是迦南人。这些是西缅的各宗族。

16利未的儿子依次是革顺哥辖米拉利利未享年一百三十七岁。 17革顺的儿子是立尼示每,二人各成宗族。 18哥辖的儿子是暗兰以斯哈希伯仑乌薛哥辖享年一百三十三岁。 19米拉利的儿子是抹利姆示。这些是利未的各宗族。 20暗兰娶了他父亲的妹妹约基别,生了亚伦摩西暗兰享年一百三十七岁。 21哥辖另一个儿子以斯哈生了可拉尼斐细基利22乌薛的儿子是米沙利以利撒反西提利23亚伦亚米拿达的女儿、拿顺的妹妹以利沙巴结婚,生了拿答亚比户以利亚撒以他玛24可拉的儿子是亚惜以利加拿亚比亚撒,这些是可拉的各宗族。 25亚伦的儿子以利亚撒普铁的一个女儿结婚,生了非尼哈。以上是利未各宗族的族长。

26正是亚伦摩西受耶和华之命,要按以色列人的宗族支派把他们带出埃及27也是这二人要求埃及王法老让他们把以色列人带出埃及28那时,耶和华曾经在埃及摩西说: 29“我是耶和华,你要把我吩咐你的一切话告诉埃及法老。” 30摩西却对耶和华说:“你看,我拙口笨舌,法老怎肯听我的话?”

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 6:1-30

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን፣ “አሁን በፈርዖን ላይ የማደርገውን ታያለህ፤ ከኀያሉ እጄ የተነሣ እንዲሄዱ ይለቅቃቸዋል፤ ከኀያሉም እጄ የተነሣ ከአገሩ ያስወጣቸዋል” አለው።

2እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ሙሴን አለው፤ “እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነኝ። 3ሁሉን የሚችል አምላክ6፥3 ዕብራይስጡ ኤልሻዳይ ይለዋል። (ኤሎሂም) ሆኜ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ ተገለጥሁላቸው፤ ነገር ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) በተባለው ስሜ6፥3 ዘፀ 3፥15 ማብ ይመ ራሴን አልገለጥሁላቸውም።6፥3 ወይም እግዚአብሔር በተባለው ስሜ ራሴን አልገለጥሁላቸውምን? 4በእንግድነት የሚኖሩባትን የከነዓንን ምድር እንድሰጣቸው ከእነርሱ ጋር ቃል ኪዳን ገብቻለሁ። 5ደግሞም በግብፃውያን ሥር በባርነት ሆነው ያሰሙትን የእስራኤላውያንን የሥቃይ ድምፅ ሰምቻለሁ ኪዳኔንም አስታውሻለሁ።

6“ስለዚህ ለእስራኤላውያን እንዲህ በላቸው፤ ‘እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነኝ፤ ከግብፃውያን ቀንበር አወጣችኋለሁ። ለእነርሱ ባሪያ ከመሆን ነጻ አወጣችኋለሁ፤ በተዘረጋች ክንድና በታላቅ ፍርድ እቤዣችኋለሁ። 7የራሴ ሕዝብ አደርጋችኋለሁ፤ እኔም አምላክ (ኤሎሂም) እሆናችኋለሁ ከግብፃውያን ቀንበር ያላቀቅኋችሁ እኔ እግዚአብሔር አምላክ (ያህዌ ኤሎሂም) መሆኔንም ታውቃላችሁ። 8ከዚያም ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ እሰጣችኋለሁ ብዬ ወደማልሁላቸው ምድር አመጣችኋለሁ፤ ርስት አድርጌ እሰጣችኋለሁ። እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነኝ።’ ”

9ሙሴ ይህን ለእስራኤላውያን ነገራቸው፤ ተስፋ ከመቍረጣቸውና ከአስከፊ እስራታቸው የተነሣ ግን አላዳመጡትም።

10ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 11“ሂድና ለግብፅ ንጉሥ ለፈርዖን እስራኤላውያን ከአገሩ እንዲወጡ ይፈቅድላቸው ዘንድ ንገረው።”

12ሙሴ ግን እግዚአብሔርን (ያህዌ)፣ “እስራኤላውያን ያልሰሙኝ፣ ፈርዖን እንዴት ይሰማኛል፤ እኔ ለራሴ ተብታባ ሰው ነኝ”6፥12 ዕብራይስጡ በዚህ ስፍራና 30 ላይ፣ ያልተገረዘ ከንፈር ይላል አለው።

የሙሴና የአሮን የትውልድ መዝገብ

13በዚህ ሁኔታ እግዚአብሔር (ያህዌ) ስለ እስራኤላውያንና ስለ ግብፅ ንጉሥ ስለ ፈርዖን ለሙሴና ለአሮን ነገራቸው፤ እስራኤላውያንንም ከግብፅ እንዲያወጡ አዘዛቸው።

14የየቤተ ሰቡ6፥14 በዚህ ስፍራና በ25 ላይ፣ ያለው ቤተ ሰብ የዕብራይስጥ ቃል ከጐሣም የበለጠ ነው። አለቆች እነዚህ ነበሩ፤

የእስራኤል የበኵር ልጅ የሮቤል ልጆች፣

ሄኖኅ፣ ፈሉስ፣ አስሮን፣ ከርሚ።

እነዚህ የሮቤል ነገድ ናቸው።

15የስምዖን ወንዶች ልጆች፣

ይሙኤል፣ ያሚን፣ ኦሃድ፣ ያኪን፣ ጾሐርና የከነዓናዊቷም ልጅ ሳኡል ነበሩ።

እነዚህ የስምዖን ነገድ አባቶች ናቸው።

16በትውልዳቸው መሠረት የሌዊ ወንዶች ልጆች ስሞች እነዚህ ነበሩ፤

ጌድሶን፣ ቀዓትና ሜራሪ ናቸው። ሌዊ መቶ ሠላሳ ሰባት ዓመት ኖረ።

17የጌድሶን ወንዶች ልጆች በትውልዳቸው ሎቤኒና ሰሜኢ ነበሩ።

18የቀዓት ወንዶች ልጆች እንበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮንና ዑዝኤል ነበሩ፤ ቀዓት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ።

19የሜራሪ ወንዶች ልጆች ሞሖሊና ሙሲ ነበሩ።

በትውልዳቸው መሠረት የሌዊ ነገዶች እነዚህ ናቸው።

20እንበረም የአጎቱን እናት ዮካብድን አገባ፤ እርሷም አሮንና ሙሴን ወለደችለት። እንበረም መቶ ሠላሳ ሰባት ዓመት ኖረ።

21የይስዓር ወንዶች ልጆች፣ ቆሬ፣ ናፌግና ዝክሪ ነበሩ።

22የዑዝኤል ወንዶች ልጆች፣ ሚሳኤል፣ ኤልዳፋንና ሥትሪ ነበሩ።

23አሮንም የአሚናዳብን ልጅ፣ የነአሶንን እኅት ኤልሳቤጥን አገባ፤ እርሷም ናዳብንና አብዩድን፣ አልዓዛርንና ኢታምርን ወለደችለት።

24የቆሬ ወንዶች ልጆች፣ አሴር፣ ሕልቃናና አብያሳፍ ነበሩ፤

እነዚህ የቆሬ ነገድ ጐሣ ናቸው።

25የአሮን ልጅ አልዓዛር ከፉትኤል ሴት ልጆች አንዷን አገባ፤ እርሷም ፊንሐስን ወለደችለት።

እነዚህ እንደየነገዳቸው የሌዋውያን ጐሣዎች አለቆች ነበሩ።

26እግዚአብሔር (ያህዌ) “እስራኤላውያንን በየሰራዊታቸው ከግብፅ አውጡ” ብሎ የነገራቸው እነዚህኑ አሮንንና ሙሴን ነበር። 27ስለ እስራኤላውያን ከግብፅ መውጣት፣ የግብፅን ንጉሥ ፈርዖንን ያናገሩትም እነዚሁ ነበሩ።

28እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን በግብፅ በተናገረው ጊዜ፣ 29እንዲህ አለው፤ “እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነኝ፤ የነገርሁህን ሁሉ ለግብፅ ንጉሥ ለፈርዖን ንገረው።”

30ሙሴ ግን እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዲህ አለው፤ “ፈርዖን ምን ብሎ ይሰማኛል? አንደበቴ ኰልታፋ ነው።”