使徒行传 6 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

使徒行传 6:1-15

选立执事

1那时,门徒的人数与日俱增。当中有些讲希腊话的犹太人埋怨讲希伯来话的犹太人,说对方在日常分配食物的事上怠慢了他们的寡妇。 2于是,十二使徒召集所有的门徒,对他们说:“我们不应该忽略传上帝的道,去管理膳食。 3弟兄姊妹,请从你们中间选出七位声誉良好、被圣灵充满、有智慧的人来负责膳食, 4而我们要专心祈祷和传道。”

5大家一致同意,便选出充满信心、被圣灵充满的司提凡,此外还有腓利伯罗哥罗尼迦挪提门巴米拿,以及曾信过犹太教、来自安提阿的外族人尼哥拉6大家将这七个人带到使徒面前。使徒把手按在他们身上,为他们祷告。

7上帝的道兴旺起来,耶路撒冷的门徒大大增多,连许多祭司也皈信了。

司提凡被捕

8司提凡得到极大的恩典和能力,在百姓中间行了惊人的神迹奇事。 9但有些来自古利奈亚历山大基利迦亚细亚、属于“自由人6:9 自由人”指的是原为奴隶,后来获得自由的人。会堂”的犹太人联合起来与司提凡辩论。 10他们无法驳倒司提凡,因为他靠着智慧和圣灵说话。

11于是,他们暗中唆使一些人诬告司提凡说:“我们听见他说亵渎摩西和上帝的话!” 12又煽动百姓、长老和律法教师抓住司提凡,把他押到公会。 13他们还派人作伪证说:“司提凡常常讲侮辱圣地6:13 圣地”指“圣殿”。和律法的话。 14我们听见他说那个拿撒勒人耶稣要毁坏圣殿,还要摒弃摩西传给我们的规矩。” 15在场的人都盯着司提凡,只见他的容貌好像天使一样。

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 6:1-15

የሰባቱ ዲያቆናት መመረጥ

1የደቀ መዛሙርት ቍጥር እየጨመረ በሄደበት በዚህ ወቅት፣ ከግሪክ አገር የመጡ አይሁድ በይሁዳ ይኖሩ በነበሩት አይሁድ ላይ አጕረመረሙ፤ ምክንያቱም በየዕለቱ በሚከናወነው ምግብ የማደል አሠራር ላይ ከእነርሱ ወገን የሆኑት መበለቶች ችላ ተብለው ነበር። 2ስለዚህ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ሌሎችን ደቀ መዛሙርት በአንድነት ሰብስበው እንዲህ አሉ፤ “እኛ የማእዱን አገልግሎት ለማስተናገድ ስንል የእግዚአብሔርን ቃል አገልግሎት መተው አይገባንም። 3ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፤ ከእናንተ መካከል በመንፈስ ቅዱስና በጥበብ የተሞሉ ለመሆናቸው የተመሰከረላቸውን ሰባት ሰዎች ምረጡ፤ ይህን ኀላፊነት ለእነርሱ እንሰጣለን፤ 4እኛ ግን በጸሎትና በቃሉ አገልግሎት እንተጋለን።”

5አባባሉ ሁላቸውን ደስ አሰኘ፤ በእምነትና በመንፈስ ቅዱስ የተሞላውን እስጢፋኖስን እንዲሁም ፊልጶስን፣ ጵሮኮሮስን፣ ኒቃሮናን፣ ጢሞናን፣ ጰርሜናንና ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን አንጾኪያዊውን ኒቆላዎስን መረጡ። 6እነዚህንም አምጥተው ሐዋርያት ፊት አቀረቧቸው፤ እነርሱም ከጸለዩ በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው።

7የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ፤ የደቀ መዛሙርቱም ቍጥር በኢየሩሳሌም እጅግ እየበዛ ሄደ፤ ከካህናትም ብዙዎቹ ለእምነት የታዘዙ ሆኑ።

የእስጢፋኖስ መያዝ

8በዚህ ጊዜ እስጢፋኖስ ጸጋንና ኀይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅ ነገሮችንና ታምራዊ ምልክቶችን ያደርግ ነበር። 9“የነጻ ወጪዎች ምኵራብ” ተብሎ የሚጠራው ምኵራብ አባላት የሆኑ ከቀሬናና ከእስክንድርያ፣ እንዲሁም ከኪልቅያና ከእስያ አውራጃዎች የመጡ ሰዎችም ተቃውሞ አስነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ጀመር፤ 10ይሁን እንጂ ይናገርበት የነበረውን ጥበብና መንፈስ መቋቋም አልቻሉም።

11ስለዚህ፣ “እስጢፋኖስ በሙሴና በእግዚአብሔር ላይ የስድብ ቃል ሲሰነዝር ሰምተናል” የሚሉ ሰዎችን በስውር አዘጋጁ።

12በዚህ ሁኔታ ሕዝቡን፣ የአገር ሽማግሌዎቹንና የሕግ መምህራኑን በማነሣሣት፣ እስጢፋኖስን አስይዘው በአይሁድ ሸንጎ ፊት አቀረቡት፤ 13እንዲህ ብለው የሚመሰክሩ የሐሰት ምስክሮችንም አቆሙበት፤ “ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራና በሕጉ ላይ የስድብ ቃል መናገሩን በፍጹም አልተወም፤ 14ምክንያቱም ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ እንደሚያጠፋና ከሙሴ የተቀበልነውን ወግ እንደሚለውጥ ሲናገር ሰምተነዋል።”

15በሸንጎው ተቀምጠው የነበሩትም ሁሉ እስጢፋኖስን ትኵር ብለው ሲመለከቱት ፊቱ የመልአክ ፊት መስሎ ታያቸው።