以赛亚书 64 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 64:1-12

1愿你裂天而降!

愿群山在你面前战抖!

2求你使敌人认识你的威名,

使列国在你面前颤抖,

如火烧干柴使水沸腾。

3你曾降临,行超乎我们预料的可畏之事,

那时群山在你面前战抖。

4自古以来,从未见过,

也未听过有任何神明像你一样为信奉他的人行奇事。

5你眷顾乐于行义、遵行你旨意的人。

我们不断地犯罪惹你发怒,

我们怎能得救呢?

6我们的善行不过像肮脏的衣服,

我们都像污秽的人,

像渐渐枯干的叶子,

我们的罪恶像风一样把我们吹去。

7无人呼求你,

无人向你求助,

因为你掩面不理我们,

让我们在自己的罪中灭亡。

8但耶和华啊,你是我们的父亲。

我们是陶泥,你是窑匠,

你亲手造了我们。

9耶和华啊,求你不要大发烈怒,

不要永远记着我们的罪恶。

我们都是你的子民,

求你垂顾我们。

10你的众圣城已沦为荒场,

甚至锡安已沦为荒场,

耶路撒冷已沦为废墟。

11我们那圣洁、华美的殿——我们祖先颂赞你的地方已被焚毁,

我们珍爱的一切都被摧毁。

12耶和华啊,你怎能坐视不理呢?

你仍然保持缄默,使我们重重地受罚吗?

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 64:1-12

1አቤቱ፤ ሰማያትን ቀድደህ ምነው በወረድህ!

ምነዋ ተራሮች በፊትህ በተናወጡ!

2እሳት ሲለኰስ ጭራሮን እንደሚያቀጣጥል፣

ውሃንም እንደሚያፈላ፣

ስምህ በጠላቶችህ ዘንድ እንዲታወቅ ውረድ፤

መንግሥታትም በፊትህ እንዲንቀጠቀጡ አድርግ።

3እኛ ያልጠበቅነውን አስፈሪ ነገር ባደረግህ ጊዜ፣

አንተ ወረድህ፤ ተራሮችም በፊትህ ተንቀጠቀጡ።

4ከጥንት ጀምሮ፣

በተስፋ ለሚጠባበቁት የሚደርስላቸው፣

እንደ አንተ ያለውን አምላክ ያየ ዐይን፣

ያደመጠ ጆሮ ፈጽሞ አልነበረም።

5በደስታ ቅን ነገር የሚያደርጉትን፣

መንገድህን የሚያስቡትንም ትረዳለህ፤

እኛ ግን በእነርሱ ላይ ሳናቋርጥ ኀጢአት በመሥራታችን፣

እነሆ፤ ተቈጣህ፤

ታዲያ እንዴት መዳን እንችላለን?

6ሁላችን እንደ ረከሰ ሰው ሆነናል፤

የጽድቅ ሥራችን እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤

ሁላችን እንደ ቅጠል ረግፈናል፤

ኀጢአታችንም እንደ ነፋስ ጠራርጎናል።

7ማንም በጸሎት ስምህን አይጠራም፤

አንተንም ለመያዝ የሚሞክር የለም፤

ፊትህን ከእኛ ሰውረሃል፤

ስለ ኀጢአታችንም ትተኸናል።

8ይህም ሆኖ፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አባታችን ነህ፤

እኛ ሸክላዎች፣ አንተም ሸክላ ሠሪ ነህ፤

ሁላችንም የእጅህ ሥራ ነን፤

9እግዚአብሔር ሆይ፤ ከልክ በላይ አትቈጣን፤

ኀጢአታችንንም ለዘላለም አታስብ፤

እባክህ ተለመነን፤ ፊትህን ወደ እኛ መልስ፤

ሁላችንም የአንተ ሕዝብ ነንና።

10የተቀደሱ ከተሞችህ ምድረ በዳ ሆኑ፤

ጽዮን ራሷ እንኳ ምድረ በዳ፣ ኢየሩሳሌምም የተፈታች ሆናለች።

11አባቶቻችን አንተን ያመሰገኑበት የተቀደሰውና የተከበረው ቤተ መቅደሳችን፣

በእሳት ተቃጥሏል፤

ያማሩ ቦታዎቻችንም ሁሉ እንዳልነበር ሆነዋል።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ ሁሉ ሆኖ አትመለስምን?

ዝም ብለህ ከልክ በላይ ትቀጣናለህን?