以赛亚书 39 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 39:1-8

巴比伦的使者

1那时,巴比伦王——巴拉但的儿子米罗达·巴拉但听说希西迦患病、后来痊愈,便派人送去书信和礼物。 2希西迦欣然接见使者,让他们观看国库里的金银、香料、珍贵膏油、所有兵器和一切宝物。希西迦把宫中及国内的一切都给他们看。

3以赛亚先知来见希西迦王,问他:“这些人说了些什么?他们从哪里来?”

希西迦答道:“他们从遥远的巴比伦来。”

4以赛亚问:“他们在你宫中看见了什么?”

希西迦答道:“他们看到了我宫中的一切。我把国库里的一切都给他们看了。”

5以赛亚希西迦说:“你听着,万军之耶和华说, 6‘终有一天,你王宫中的一切和你祖先积攒到现在的一切,必一件不留地被掳到巴比伦。这是耶和华说的。 7你的子孙当中必有人被掳去,在巴比伦王的宫中做太监。’” 8希西迦以赛亚说:“耶和华借你说的话很好。”因为他想:“我有生之年将平安稳妥。”

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 39:1-8

ከባቢሎን የመጡ መልእክተኞች

1በዚያን ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ፣ የባልዳን ልጅ፣ መሮዳክ ባልዳን የሕዝቅያስን መታመምና መፈወስ ሰምቶ ስለ ነበር፣ ደብዳቤና ስጦታ ላከለት። 2ሕዝቅያስም መልእክተኞቹን በደስታ ተቀበለ፤ ለእነርሱም በግምጃ ቤቱ ውስጥ ያለውን ብሩን፣ ወርቁን፣ ቅመማ ቅመሙን፣ ምርጡን ዘይት እንዲሁም የጦር መሣሪያውን በሙሉ፣ ያለውንም ንብረት አንዳች ሳያስቀር አሳያቸው። በቤተ መንግሥቱም ሆነ በግዛቱ ሁሉ ሕዝቅያስ ያላሳያቸው ነገር አልነበረም።

3ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ ንጉሡ ሕዝቅያስ መጥቶ፣ “እነዚያ ሰዎች ምን አሉህ? ወደ አንተ ዘንድ የመጡትስ ከየት ነው?” አለው።

ሕዝቅያስም፣ “ወደ እኔ የመጡት ከሩቅ አገር፣ ከባቢሎን ነው” አለው።

4ነቢዩም፣ “በቤተ መንግሥትህ ያዩት ምንድን ነው?” አለው።

ሕዝቅያስም፣ “በቤተ መንግሥቴ ያለውን ሁሉ አይተዋል፤ ከንብረቴ ያላሳየኋቸው ምንም ነገር የለም” አለ።

5ኢሳይያስም ሕዝቅያስን እንዲህ አለው፤ “የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ 6እነሆ፤ በቤተ መንግሥትህ ያለው ሁሉ፣ አባቶችህ እስከዚህች ቀን ድረስ ያከማቹትም ሁሉ ወደ ባቢሎን ተማርኮ የሚወሰድበት ቀን ይመጣል፤ አንዳች የሚተርፍ ነገር የለም፤ ይላል እግዚአብሔር7ከአብራክህ ከሚከፈሉት፣ ከዘርህ፣ ከአንተ ከሚወለዱት ልጆች ተወስደው፣ በባቢሎን ንጉሥ ቤተ መንግሥት ጃንደረባዎች ይሆናሉ።”

8ሕዝቅያስም፣ “የተናገርኸው የእግዚአብሔር ቃል መልካም ነው” አለው፤ “በዘመኔ ሰላምና ጸጥታ ከኖረ ዘንድ” ብሎ ዐስቦ ነበርና።