以斯拉记 6 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以斯拉记 6:1-22

发现塞鲁士王的谕旨

1于是,大流士王下令查阅保存在巴比伦库房里的典籍。 2玛代亚马他城的宫内找到一卷书,书中记载如下:

3塞鲁士王元年,塞鲁士王就耶路撒冷的上帝之殿降下谕旨,要重建这殿作献祭之处,要奠立殿的地基。殿要高二十七米、宽二十七米, 4每三层巨石加铺一层木料,经费由国库支付。 5尼布甲尼撒耶路撒冷上帝的殿里掳到巴比伦的金银器皿,都要归还到耶路撒冷上帝的殿里,放回原处。”

6于是,大流士王降旨:

“河西总督达乃示他·波斯乃,以及你们的同僚——河西的官员,要远离那殿! 7不要干涉上帝殿的建造,要让犹太人的省长和长老在原址上重建这座上帝的殿。 8另外,我降旨命你们帮助犹太人的长老建造上帝的殿,要立刻从河西的王室税收中拨出款项作建殿之用,以免耽误工程。 9他们向天上的上帝献燔祭时所需的公牛犊、公绵羊、绵羊羔、小麦、盐、酒和油,都要照耶路撒冷祭司的话天天供给他们,不得有误, 10好让他们向天上的上帝献上蒙悦纳的祭物,并为王和众王子求寿。 11我再降旨,若有人更改这谕旨,必从他的房屋抽掉一根大梁,把他钉在梁上挂起来,他的房屋也要沦为粪堆。 12无论君王还是百姓,若有人擅自更改这命令或毁坏耶路撒冷的这殿,愿拣选这殿作其居所的上帝毁灭他!我大流士降此谕旨,务要速速遵行。”

建殿工程竣工

13于是,河西总督达乃示他·波斯乃及其同僚都认真执行大流士王的谕旨。 14哈该先知和易多的子孙撒迦利亚的劝勉下,犹太人的长老建造这殿,进展顺利。他们遵照上帝的命令和波斯塞鲁士大流士亚达薛西的谕旨,完成了建殿工程。 15大流士王第六年亚达月6:15 亚达月”即希伯来历的十二月,阳历是二月中旬到三月中旬。三日,建殿工程竣工。

举行献殿礼

16以色列人、祭司、利未人,以及其余流亡归来的人都满心欢喜地为上帝的殿举行奉献礼。 17他们为此献上一百头公牛犊,二百只公绵羊和四百只绵羊羔,又照以色列十二支派的数目献上十二只公山羊,作全体以色列人的赎罪祭。 18他们依照摩西律法书的规定,派祭司和利未人按班次在耶路撒冷事奉上帝。

守逾越节

19一月十四日,流亡归来的人守逾越节。 20祭司和利未人一起自洁,成为洁净的人,并为所有流亡归来的人、其他祭司同胞以及他们自己宰杀逾越节的羔羊。 21从流亡之地归回的以色列人,连同所有弃绝当地民族的污秽行为、寻求以色列的上帝耶和华的人,一起吃这羔羊。 22他们欢欢喜喜地守除酵节七天,因为耶和华使亚述王对他们心存善意,帮助他们重建以色列上帝的殿。

New Amharic Standard Version

ዕዝራ 6:1-22

የዳርዮስ ዐዋጅ

1ከዚያም ንጉሥ ዳርዮስ በባቢሎን ግምጃ ቤት የተቀመጡት መዛግብት እንዲመረመሩ ትእዛዝ ሰጠ። 2በሜዶን አውራጃ በሚገኘው በአሕምታ ከተማ አንድ ጥቅልል ብራና ተገኘ፤ በውስጡም እንዲህ የሚል ቃል ተጽፎበት ነበር፤

ማስታወሻ፤

3በንጉሥ ቂሮስ የመጀመሪያው ዓመት በኢየሩሳሌም ስለሚገኘው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ንጉሡ የሰጠው ትእዛዝ ይህ ነው፤ ቤተ መቅደሱ መሥዋዕት የሚቀርብበት ቦታ ሆኖ እንደ ገና ይሠራ፤ መሠረቱም ይጣል፤ ቁመቱ ስድሳ ክንድ6፥3 27 ሜትር ያህል ነው።፣ ወርዱም ስድሳ ክንድ ይሁን፤ 4በሦስት ዙር ታላላቅ ድንጋዮችና በአንድ ዙር ዕንጨት ይሠራ፤ ወጪውም ከቤተ መንግሥቱ ግምጃ ቤት ይከፈል። 5እንዲሁም ናቡከደነፆር በኢየሩሳሌም ከሚገኘው ቤተ መቅደስ አውጥቶ ወደ ባቢሎን የወሰዳቸው የእግዚአብሔር ቤት የወርቅና የብር ዕቃዎች፣ በኢየሩሳሌም ወዳለው ቦታቸው ወደ ቤተ መቅደሱ እንዲመለሱ ይሁን፤ በእግዚአብሔርም ቤት ይቀመጡ።

6አሁንም በኤፍራጥስ ማዶ አገረ ገዥ የሆንኸው ተንትናይ፣ ሰተርቡዝናይና እናንተም በዚያ አውራጃ የምትገኙ ተባባሪዎቻቸው ሁሉ ወደዚያ አትድረሱ። 7በዚህም በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሥራ ጣልቃ አትግቡ፤ ይህን የእግዚአብሔርን ቤት የአይሁድ አገረ ገዥና የአይሁድ መሪዎች በቀድሞው ቦታ ላይ መልሰው ይሥሩት።

8በተጨማሪም የአይሁድ መሪዎች ይህን የእግዚአብሔር ቤት እንደ ገና ሲሠሩ፣ እናንተ ምን እንደምታደርጉላቸው ይህን ትእዛዝ ሰጥቻለሁ፤ ሥራውም እንዳይቋረጥ የእነዚህ ሰዎች ወጪ በሙሉ ከመንግሥት ግምጃ ቤትና ከኤፍራጥስ ማዶ ከሚገኘው ገቢ ላይ ይከፈል። 9ለሰማይ አምላክ የሚቃጠል መሥዋዕት ይሆን ዘንድ የሚያስፈልጋቸውን ነገር፣ ማለት ወይፈኖችን፣ አውራ በጎችንና ተባዕት ጠቦቶችን ስጧቸው፤ እንዲሁም ስንዴው፣ ጨዉ፣ የወይን ጠጁና ዘይቱ በኢየሩሳሌም ያሉት ካህናት በሚጠይቋችሁ መሠረት ያለ ማቋረጥ በየቀኑ ይሰጣቸው። 10ይህ የሚሆነው የሰማይ አምላክን ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት እንዲያቀርቡ፣ ለንጉሡና ለወንድ ልጆቹም ደኅንነት እንዲጸልዩ ነው።

11ደግሞም ይህን ትእዛዝ የሚለውጥ ማንም ሰው ቢኖር፣ ከቤቱ ምሰሶ ተነቅሎ በምሰሶው ላይ እንዲሰቀል፣ ስለ ወንጀሉም ቤቱ የቈሻሻ መጣያ እንዲሆን አዝዣለሁ። 12ይህን ትእዛዝ ለማፍረስ ወይም በኢየሩሳሌም የሚገኘውን ቤተ መቅደስ ለማጥፋት እጁን የሚያነሣ ማንኛውንም ንጉሥ ወይም ሕዝብ፣ ስሙን በዚያ እንዲኖር ያደረገ አምላክ ያጥፋው።

እኔ ዳርዮስ በትጋት እንዲፈጸም ይህን ትእዛዝ ሰጥቻለሁ።

የቤተ መቅደሱ ሥራ ፍጻሜና ምረቃ

13ከዚያም ንጉሡ ዳርዮስ ባዘዘው መሠረት በኤፍራጥስ ማዶ አገረ ገዥ የነበረው ተንትናይ፣ ሰተርቡዝናይና ተባባሪዎቻቸው ሥራው በትጋት እንዲፈጸም አደረጉ። 14ስለዚህ የአይሁድ መሪዎች በነቢዩ በሐጌና በአዶ ልጅ በዘካርያስ ትንቢት እየተጽናኑ ሥራውን ቀጠሉ፤ የቤተ መቅደሱንም ሥራ በእስራኤል አምላክ ትእዛዝ እንዲሁም የፋርስ ነገሥታት ቂሮስ፣ ዳርዮስና አርጤክስስ በሰጡት ትእዛዝ መሠረት ሠርተው ጨረሱ። 15ይህም ቤተ መቅደስ ንጉሥ ዳርዮስ በነገሠ በስድስተኛው ዓመት አዳር ተብሎ በሚጠራው ወር በሦስተኛው ቀን ተጠናቀቀ።

16ከዚያም የእስራኤል ሕዝብ፣ ካህናቱ፣ ሌዋውያኑና የቀሩትም ምርኮኞች የእግዚአብሔርን ቤት ምረቃ በዓል በደስታ አከበሩ። 17ለዚህ ለእግዚአብሔር ቤት ምረቃም አንድ መቶ ወይፈኖችን፣ ሁለት መቶ አውራ በጎችንና አራት መቶ ተባዕት ጠቦቶችን ሰጡ፤ ለመላው እስራኤል የኀጢአት መሥዋዕትም ዐሥራ ሁለት ተባዕት ፍየሎችን በእያንዳንዱ የእስራኤል ነገድ ልክ አቀረቡ። 18በሙሴ መጽሐፍ በተጻፈው መሠረት በኢየሩሳሌም ላለው ለእግዚአብሔር አገልግሎት ካህናቱን በየማዕረጋቸው፣ ሌዋውያኑንም በየክፍላቸው መደቧቸው።

የፋሲካ በዓል

19ምርኮኞቹ በመጀመሪያው ወር በዐሥራ አራተኛው ቀን የፋሲካን በዓል አከበሩ። 20ካህናቱና ሌዋውያኑ ራሳቸውን አነጹ፤ ሁሉም በሥርዐቱ መሠረት ነጽተው ነበር። ሌዋውያኑም የፋሲካውን በግ ለምርኮኞቹ ሁሉ፣ ለካህናት ወንድሞቻቸውና ለራሳቸው ዐረዱ። 21ስለዚህ ከምርኮ የተመለሱት እስራኤላውያን የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን በአምልኮ ይፈልጉት ዘንድ ራሳቸውን ከአረማውያን ጎረቤቶቻቸው ርኩሰት ከለዩት ሁሉ ጋር በሉ። 22እግዚአብሔር ደስ እንዲሰኙ ስላደረጋቸው የቂጣን በዓል ሰባት ቀን በደስታ አከበሩ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር የአሦርን ንጉሥ ልብ ለውጦ በእስራኤል አምላክ በእግዚአብሔር ቤት ሥራ እንዲያግዛቸው አድርጎ ነበር።