以弗所书 5 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以弗所书 5:1-33

行事与圣徒的身份相称

1因此,你们既然是上帝疼爱的儿女,就要效法上帝。 2要以爱心待人,像基督爱我们一样,祂为我们牺牲自己作为献给上帝的馨香供物和祭物。

3一切淫乱、污秽或贪婪的事在你们当中连提都不要提,才合乎圣徒的身份。 4污言秽语、愚昧粗俗的谈笑都不合宜,总要说感恩的话才好。 5因为你们清楚知道,淫乱的人、污秽的人,还有贪婪的人,就是拜偶像的人,在基督和上帝的国里没有立足之地。 6不要被虚空的道理欺骗,因为上帝的烈怒必临到上述那些悖逆的人。 7所以,你们不要与他们同流合污。

8你们从前活在黑暗中,现在既然活在主的光明中,行事为人就该像光明的儿女。 9光明总是结出良善、公义和真理的果子。 10你们要察验什么是主所喜悦的事, 11不可参与那些黑暗无益的事,反要揭发斥责, 12因为那些人暗地里做的事就是提起来都觉得可耻。 13然而,一切的事被光一照,都会真相大白, 14因为光能使一切显明出来。因此有人说:

“沉睡的人啊,醒来吧!

从死人中起来吧,

基督要光照你了!”

15因此,你们要注意自己的生活,不要像愚昧人,要像有智慧的人。 16要爱惜光阴,因为现今是个邪恶的世代。 17所以,不要做糊涂人,要明白主的旨意。 18不要醉酒,醉酒会使人放荡,要被圣灵充满。 19要用诗篇、圣乐、灵歌互相激励,从心底唱出赞美主的旋律。 20凡事总要奉我们主耶稣基督的名感谢父上帝。

夫妇之道

21你们要存敬畏基督的心彼此顺服。

22做妻子的要顺服自己的丈夫,如同顺服主基督。 23因为丈夫是妻子的头,正如基督是祂的身体——教会的头,又是教会的救主。 24教会怎样顺服基督,妻子也要照样凡事顺服丈夫。

25做丈夫的要爱妻子,正如基督爱教会,为教会舍己, 26好借着自己的道用水洗净教会,使她圣洁, 27以便把圣洁、完美、没有污点、皱纹等瑕疵的荣耀教会呈献给祂自己。 28同样,做丈夫的也要爱妻子如同爱自己的身体,爱妻子就是爱自己。 29没有人会厌恶自己的身体,人总是珍惜保养身体,正如基督对待教会一样, 30因为我们是祂身上的肢体。 31“因此,人要离开父母,与妻子结合,二人成为一体。” 32这是一个极大的奥秘,然而我是指着基督和教会的关系说的。 33总之,你们做丈夫的都要爱妻子如同爱自己,做妻子的也要敬重丈夫。

New Amharic Standard Version

ኤፌሶን 5:1-33

1እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን ምሰሉ፤ 2ክርስቶስ እንደ ወደደን ራሱንም ስለ እኛ መልካም መዐዛ ያለው መባና መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር እንደ ሰጠ እናንተም በፍቅር ተመላለሱ።

3ማንኛውም የዝሙት ወይም የርኩሰት ወይም የሥሥት ነገር ከቶ በመካከላችሁ አይነሣ፤ ይህ ቅዱስ ለሆነው ለእግዚአብሔር ሕዝብ አይገባምና። 4የሚያሳፍርና ተራ የሆነ ንግግር፣ ዋዛ ፈዛዛም ለእናንተ ስለማይገባ በመካከላችሁ አይኑር፤ ይልቁንስ የምታመሰግኑ ሁኑ። 5ደግሞም ይህን ዕወቁ፤ ማንም አመንዝራ ወይም ርኩስ ወይም ስግብግብ፣ ይኸውም ጣዖት አምላኪ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት5፥5 ወይም የክርስቶስና የእግዚአብሔር መንግሥት በሆነው ርስት የለውም። 6ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ የሚመጣው በእንደዚህ ዐይነት ነገር ነው። 7ስለዚህ እንዲህ ካሉ ጋር አትተባበሩ።

8ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ፤ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ። እንደ ብርሃን ልጆች ኑሩ፤ 9የብርሃኑ ፍሬ በበጎነት፣ በጽድቅና በእውነት ሁሉ ዘንድ ነውና። 10እንዲሁም ጌታን ደስ የሚያሰኘውን ፈልጉ። 11ፍሬ ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር ምንም ዐይነት ግንኙነት አይኑራችሁ፤ ይልቁን ግለጡት፤ 12በድብቅ የሚሠሩትን ነገር መናገር ራሱ አሳፋሪ ነውና። 13ብርሃን የበራበት ነገር ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤ 14ምክንያቱም ሁሉን ነገር እንዲታይ የሚያደርገው ብርሃን ነውና፤ ስለዚህም፣

“አንተ የተኛህ ንቃ፤

ከሙታን ተነሣ፤

ክርስቶስም ያበራልሃል” ተብሏል።

15እንግዲህ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንደ ጥበበኞች እንዴት እንደምትኖሩ ተጠንቀቁ። 16ቀኖቹ ክፉ ናቸውና ዘመኑን በሚገባ ዋጁ። 17ስለዚህ ሞኞች አትሁኑ፤ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ። 18በመንፈስ ተሞሉ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ ብክነት ነውና። 19በመዝሙርና በውዳሴ፣ በመንፈሳዊም ዝማሬ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ በልባችሁ ለጌታ ተቀኙ፤ አዚሙም። 20በዚህም እግዚአብሔር አብን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ሁሉ ነገር ሁልጊዜ አመስግኑ።

21ለክርስቶስ ካላችሁ አክብሮታዊ ፍርሀት የተነሣ አንዳችሁ ለአንዳችሁ ተገዙ።

ባልና ሚስት

5፥22–6፥9 ተጓ ምብ – ቈላ 3፥18–4፥1

22ሚስቶች ሆይ፤ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁም ተገዙ 23ክርስቶስ፣ አካሉ ለሆነችውና አዳኟ ለሆናት ቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ ሁሉ፣ ባልም የሚስቱ ራስ ነውና። 24እንግዲህ ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ፣ ሚስቶችም ለባሎቻቸው በማንኛውም ነገር እንደዚሁ መገዛት ይገባቸዋል።

25ባሎች ሆይ፤ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳትና ራሱንም ስለ እርሷ አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ እናንተም ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ 26በቃሉ አማካይነት በውሃ ዐጥቦ በማንጻት እንድትቀደስ፣ 27እንዲሁም ጕድፍ ወይም የፊት መጨማደድ ወይም አንዳች እንከን ሳይገኝባት ቅድስትና ነውር አልባ የሆነች ክብርት ቤተ ክርስቲያን አድርጎ ለራሱ ሊያቀርባት ነው። 28ባሎችም እንደዚሁ ሚስቶቻቸውን እንደ ገዛ ሥጋቸው መውደድ ይገባቸዋል። ሚስቱን የሚወድድ ራሱን ይወድዳል። 29የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ማንም የለም፤ ይመግበዋል፤ ይንከባከበዋል፤ ክርስቶስም ለቤተ ክርስቲያን ያደረገው ልክ እንደዚሁ ነው፤ 30እኛ የክርስቶስ አካል ብልቶች ነንና። 31“ስለዚህም ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ ከሚስቱም ጋር አንድ ይሆናል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ”። 32ይህ ጥልቅ ምስጢር ነው፤ እኔም ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እናገራለሁ። 33ሆኖም ከእናንተ እያንዳንዱ ሚስቱን እንደ ራሱ አድርጎ ይውደድ፤ ሚስትም ባሏን ታክብር።