Psaltaren 146 – NUB & NASV

Swedish Contemporary Bible

Psaltaren 146:1-10

Psalm 146

Herrens eviga trofasthet

1Halleluja!

Lova Herren, min själ!

2Jag vill prisa Herren så länge jag lever,

lovsjunga min Gud så länge jag finns till.

3Lita inte på de mäktiga,

på människor som inte kan rädda.

4När människans ande lämnar henne

återvänder hon till stoftet,

och alla hennes planer blir om intet.

5Men lycklig är den som väntar på hjälp från Jakobs Gud,

och hoppas på Herren, sin Gud.

6Han har gjort himlen och jorden,

haven och allt som finns i dem.

Hans trofasthet består för evigt.

7Han skaffar rätt åt de förtryckta

och ger mat till de hungriga.

Herren befriar fångarna.

8Herren öppnar de blindas ögon.

Herren lyfter upp de nerböjda.

Herren älskar de rättfärdiga.

9Herren skyddar främlingar

och har omsorg om faderlösa och änkor,

men de gudlösas planer hindrar han.

10Herren är kung för evigt, din Gud, Sion,

från generation till generation.

Halleluja!

New Amharic Standard Version

መዝሙር 146:1-10

መዝሙር 146

ለረድኤት አምላክ ምስጋና

1ሃሌ ሉያ።146፥1 አንዳንዶች ከቍጥር 10 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

ነፍሴ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኪ።

2በምኖርበት ዘመን ሁሉ እግዚአብሔርን

አመሰግናለሁ፤

በሕይወትም እስካለሁ ለአምላኬ እዘምራለሁ።

3በገዦች አትታመኑ፤ ማዳን በማይችሉ ሥጋ ለባሾችም አትመኩ።

4መንፈሳቸው ትወጣለች፤ ወደ መሬታቸውም ይመለሳሉ፤

ያን ጊዜም ዕቅዳቸው እንዳልነበር ይሆናል።

5ረዳቱ የያዕቆብ አምላክ የሆነ፣

ተስፋውንም በአምላኩ በእግዚአብሔር ላይ የጣለ ሰው ምስጉን ነው፤

6እርሱ ሰማይንና ምድርን፣ ባሕርንም፣

በእነዚህም ውስጥ ያለውን ሁሉ የፈጠረ፣

ታማኝነቱንም ለዘላለም የሚጠብቅ ነው፤

7ለተበደሉት የሚፈርድ፣

ለተራቡት ምግብን የሚሰጥ እርሱ ነው፤

እግዚአብሔር እስረኞችን ከእስራት ያወጣል፤

8እግዚአብሔር የዕውራንን ዐይን ያበራል፤

እግዚአብሔር የተዋረዱትን ከፍ ያደርጋል፤

እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል፤

9እግዚአብሔር ስደተኞችን ይጠብቃል፤

ድኻ ዐደጎችንና መበለቶችን ይደግፋል፤

የክፉዎችን መንገድ ግን ያጠፋል።

10እግዚአብሔር ለዘላለም ይነግሣል፤

ጽዮን ሆይ፤ አምላክሽ ለትውልድ ሁሉ ንጉሥ ነው።

ሃሌ ሉያ።