Hosea 1 – NUB & NASV

Swedish Contemporary Bible

Hosea 1:1-11

Hoseas äktenskap – en symbol

(1:1—3:5)

1Detta är Herrens ord som kom till Hosea, Beeris son, när Ussia, Jotam, Achas och Hiskia var kungar i Juda och Jerobeam, Joashs son, regerade i Israel.

Hoseas familj

2Så här börjar Herrens tal genom Hosea. Herren sa till honom: ”Gå och skaffa dig en sköka till hustru och barn som föds i otukt, för landet bedriver otukt gentemot Herren.” 3Han gifte sig då med Gomer, dotter till Divlajim, och hon blev med barn och födde honom en son. 4Herren sa till honom: ”Ge honom namnet Jisreel, för snart ska jag straffa Jehus släkt för hans massaker i Jisreel och göra slut på Israels kungadöme. 5Den dagen ska jag bryta sönder Israels båge i Jisreels dal.”

6Hon blev åter med barn och födde en dotter. Herren sa till Hosea: ”Ge henne namnet Lo Ruchama, för jag ska inte längre förbarma mig över israeliterna så att jag förlåter dem.1:6 Lo Ruchama betyder hon som inte får förbarmande (Lo är en negation). I slutet av versen (förlåter ) är grundtextens innebörd osäker. 7Men jag ska förbarma mig över Juda folk och rädda dem genom Herren, deras Gud. Jag ska inte rädda dem genom båge eller svärd, strid, hästar eller ryttare.”

8När Gomer hade slutat amma Lo Ruchama, blev hon med barn igen och födde en son. 9Herren sa: ”Ge honom namnet Lo Ammi1:9 Betyder inte mitt folk., för ni är inte mitt folk och jag finns inte till för er.

10Men antalet israeliter ska bli som sandkornen på havsstranden, omöjliga att mäta och räkna. Där det nu sägs till dem: ’Ni är inte mitt folk’, där ska de kallas ’Den levande Gudens barn.’ 11Då ska Juda och Israels folk förenas och ha en gemensam ledare. De ska växa upp ur landet, och Jisreels dag blir stor.

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 1:1-11

1በይሁዳ ነገሥታት በዖዝያን፣ በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን እንዲሁም በእስራኤል ንጉሥ በዮአስ1፥1 በዕብራይስጥ ዮአስ የሚለው ቃል የኢዮአስ አማራጭ ትርጕም ነው ልጅ በኢዮርብዓም ዘመን ወደ ብኤሪ ልጅ ወደ ሆሴዕ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

የሆሴዕ ሚስትና ልጆቹ

2እግዚአብሔር በሆሴዕ መናገር በጀመረ ጊዜ፣ እግዚአብሔር “ምድሪቱ ከእግዚአብሔር ተለይታ ታላቅ ምንዝርና እያደረገች ስለሆነ፣ ሄደህ አመንዝራ ሴት አግባ፤ የምንዝርና ልጆችንም ለራስህ ውሰድ” አለው። 3ስለዚህ እርሱ የዴቤላይምን ሴት ልጅ ጎሜርን አገባ፤ እርሷም ፀነሰች፤ ወንድ ልጅም ወለደችለት።

4እግዚአብሔርም ሆሴዕን እንዲህ አለው፤ “በኢይዝራኤል ስለ ተፈጸመው ግድያ የኢዩን ቤት በቅርቡ ስለምቀጣና የእስራኤልንም መንግሥት እንዲያከትም ስለማደርግ፣ ስሙን ኢይዝራኤል ብለህ ጥራው። 5በዚያም ቀን በኢይዝራኤል ሸለቆ፣ የእስራኤልን ቀስት እሰብራለሁ።”

6ጎሜር እንደ ገና ፀነሰች፤ ሴት ልጅም ወለደች፤ እግዚአብሔርም ሆሴዕን እንዲህ አለው፤ “ይቅር እላቸው ዘንድ ለእስራኤል ቤት ከእንግዲህ ስለማልራራላቸው፣ ስሟን ሎሩሃማ1፥6 ሎሩሃማ ማለት ያልተወደደች ማለት ነው ብለህ ጥራት። 7ነገር ግን ለይሁዳ ቤት እራራለሁ፤ በቀስት ወይም በሰይፍ ወይም በጦርነት ወይም በፈረሶችና በፈረሰኞች ሳይሆን በአምላካቸው በእግዚአብሔር አድናቸዋለሁ።”

8ጎሜር፣ ሎሩሃማን ጡት ካስጣለች በኋላ ሌላ ወንድ ልጅ ወለደች። 9እግዚአብሔርም እንዲህ አለው፤ “ሎዓሚ1፥9 ሎዓሚ ማለት ሕዝቤ አይደለም ማለት ነው ብለህ ጥራው፤ ምክንያቱም እናንተ ሕዝቤ አይደላችሁም፤ እኔም አምላካችሁ አይደለሁምና።

10“ይሁን እንጂ እስራኤላውያን ሊሰፈርና ሊቈጠር እንደማይችል እንደ ባሕር አሸዋ ይሆናሉ፤ ‘ሕዝቤ አይደላችሁም’ በተባሉበት ቦታ፣ ‘የሕያው አምላክ ልጆች’ ተብለው ይጠራሉ። 11የይሁዳ ሕዝብና የእስራኤል ሕዝብ እንደ ገና አንድ ይሆናሉ፤ አንድ መሪም ይሾማሉ፤ አንድ ሆነውም በምድሪቱ ይገንናሉ፤ የኢይዝራኤል ቀን ታላቅ ይሆናልና።