Isaiah 4 – NIVUK & NASV

New International Version – UK

Isaiah 4:1-6

1In that day seven women

will take hold of one man

and say, ‘We will eat our own food

and provide our own clothes;

only let us be called by your name.

Take away our disgrace!’

The Branch of the Lord

2In that day the Branch of the Lord will be beautiful and glorious, and the fruit of the land will be the pride and glory of the survivors in Israel. 3Those who are left in Zion, who remain in Jerusalem, will be called holy, all who are recorded among the living in Jerusalem. 4The Lord will wash away the filth of the women of Zion; he will cleanse the bloodstains from Jerusalem by a spirit4:4 Or the Spirit of judgment and a spirit4:4 Or the Spirit of fire. 5Then the Lord will create over all of Mount Zion and over those who assemble there a cloud of smoke by day and a glow of flaming fire by night; over everything the glory4:5 Or over all the glory there will be a canopy. 6It will be a shelter and shade from the heat of the day, and a refuge and hiding-place from the storm and rain.

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 4:1-6

1በዚያን ቀን ሰባት ሴቶች

አንዱን ወንድ ይዘው፣

“የራሳችንን ምግብ እንበላለን፤

የራሳችንንም ልብስ እንለብሳለን፤

በአንተ ስም ብቻ እንጠራና፣

ውርደታችንን አስቀርልን” ይሉታል።

የእግዚአብሔር ዛፍ ቅርንጫፍ

2በዚያን ቀን የእግዚአብሔር ዛፍ ቅርንጫፍ ያማረና የከበረ ይሆናል፤ የምድሪቱም ፍሬ ከጥፋት ለተረፈው የእስራኤል ወገን ኵራትና ክብር ይሆናል። 3በጽዮን የቀሩት፣ በኢየሩሳሌምም የተረፉት፣ በኢየሩሳሌም በሕይወት ከተመዘገቡት ሁሉ ጋር ቅዱሳን ተብለው ይጠራሉ። 4ጌታ የጽዮንን ሴቶች እድፍ ያጥባል፤ ኢየሩሳሌምንም ከተነከረችበት ደም በፍርድና በሚያቃጥል መንፈስ4፥4 ወይም በእግዚአብሔር መንፈስ ማለት ነው። ያነጻታል። 5ከዚያም እግዚአብሔር በጽዮን ተራራ ላይና በዚያ በሚሰበሰቡትም ሁሉ ላይ በቀን ደመናንና ጢስን፣ በሌሊትም የሚንበለበለውን የእሳት ብርሃን ይፈጥራል፤ በክብሩ ሁሉ ላይ መጋረጃ ይሆናል፤ 6ከቀኑ ሙቀት ጥላና መከለያ፣ ከውሽንፍርና ከዝናብም መጠጊያና መሸሸጊያ ስፍራ ይሆናል።