نشيد الأنشاد 3 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

نشيد الأنشاد 3:1-11

1(الْمَحْبُوبَةُ): طَوَالَ اللَّيْلِ عَلَى مَضْجَعِي طَلَبْتُ بِشَوْقٍ مَنْ تُحِبُّهُ نَفْسِي، فَمَا وَجَدْتُهُ. 2سَأَنْهَضُ الآنَ أَطُوفُ فِي الْمَدِينَةِ وَأَتَجَوَّلُ فِي شَوَارِعِهَا وَسَاحَاتِهَا، أَلْتَمِسُ مَنْ تُحِبُّهُ نَفْسِي. وَهَكَذَا رُحْتُ أَلْتَمِسُهُ فَمَا وَجَدْتُهُ. 3وَعَثَرَ عَلَيَّ الْحُرَّاسُ الْمُتَجَوِّلُونَ فِي الْمَدِينَةِ، فَسَأَلْتُ: أَشَاهَدْتُمْ مَنْ تُحِبُّهُ نَفْسِي؟ 4وَمَا كِدْتُ أَتَجَاوَزُهُمْ حَتَّى وَجَدْتُ مَنْ تُحِبُّهُ نَفْسِي، فَتَشَبَّثْتُ بِهِ وَلَمْ أُطْلِقْهُ حَتَّى أَدْخَلْتُهُ بَيْتَ أُمِّي وَمُخْدَعَ مَنْ حَمَلَتْ بِي. 5أَسْتَحْلِفُكُنَّ يَا بَنَاتِ أُورُشَلِيمَ بِظِبَاءِ الصَّحْرَاءِ وَأَيَائِلِهَا أَلّا تُوْقِظْنَ أَوْ تُنَبِّهْنَ الْحَبِيبَ حَتَّى يَشَاءَ.

6(نَشِيدُ بَنَاتِ أُورُشَلِيمَ): مَنْ هَذِهِ الصَّاعِدَةُ مِنَ الْقَفْرِ كَأَعْمِدَةٍ مِنْ دُخَانٍ مُعَطَّرَةٍ بِالْمُرِّ وَاللُّبَانِ وَكُلِّ عُطُورِ التَّاجِرِ؟

7هَا هِيَ أَرِيكَةُ سُلَيْمَانَ يَحِفُّ بِهِ سِتُّونَ بَطَلاً مِنْ جَبَابِرَةِ إِسْرَائِيلَ. 8جَمِيعُهُمْ مُدَجَّجُونَ بِالسُّيُوفِ مُتَمَرِّسُونَ عَلَى الْحَربِ، تَتَدَلَّى سُيُوفُهُمْ عَلَى جَوَانِبِهِمْ تَأَهُّباً لأَهْوَالِ اللَّيْلِ.

9قَدْ صَنَعَ الْمَلِكُ سُلَيْمَانُ كُرْسِيَّ الْعَرْشِ مِنْ خَشَبِ لُبْنَانَ. 10وَصَنَعَ أَعْمِدَتَهُ فِضَّةً وَمُتَّكَأَهُ ذَهَباً وَمَقْعَدَهُ أُرْجُوَاناً، وَغِطَاؤُهْ الدَّاخِلِيُّ رَصَّعَتْهُ بَنَاتُ أُورُشَلِيمَ مَحَبَّةً.

11(الْمَحْبُوبَةُ): اُخْرُجْنَ يَا بَنَاتِ صِهْيَوْنَ وَانْظُرْنَ الْمَلِكَ سُلَيْمَانَ مُكَلَّلاً بِالتَّاجِ الَّذِي تَوَّجَتْهُ بِهِ أَمُّهُ فِي يَوْمِ عُرْسِهِ، فِي يَوْمِ بَهَجَةِ قَلْبِهِ.

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 3:1-11

1ሌሊቱን ሙሉ በዐልጋዬ ላይ ሆኜ፣

ውዴን ተመኘሁ፤

ተመኘሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

2ተነሥቼ ወደ ከተማዪቱ እወጣለሁ፤

በዋና ዋና መንገዶችና በአደባባዮች እዘዋወራለሁ፤

ውዴንም እፈልገዋለሁ፤

ስለዚህም ፈለግሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

3በከተማዪቱ ውስጥ ሲዘዋወሩ፣

የከተማዪቱ ጠባቂዎች አገኙኝ፤

እኔም፣ “ውዴን አይታችኋል?”

አልኋቸው።

4ከእነርሱ ጥቂት ዕልፍ እንዳልሁ፣

ውዴን አገኘሁት፤ ያዝሁት፤

ወደ እናቴ ቤት እስካመጣው፣

በማሕፀን ወደ ተሸከመችኝም ዕልፍኝ

እስካገባው ድረስ አልለቀውም።

5እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፤

ራሱ እስኪፈልግ ድረስ፣

ፍቅርን እንዳታስነሡት ወይም እንዳትቀሰቅሱት፣

በሚዳቋና በሜዳ ዋሊያ አማጥናችኋለሁ።

6ከከርቤና ከዕጣን፣

ከነጋዴም ቅመማ ቅመም ሁሉ በተዘጋጀ ሽቱ፣

መዐዛዋ የሚያውድ፣

እንደ ጢስ ዐምድ ከምድረ በዳ የምትወጣው ይህች ማን ናት?

7እነሆ፤ የሰሎሞን ሠረገላ

በታዋቂዎቹ የእስራኤል መኳንንት፣

ስድሳ ጦረኞች ታጅባለች፤

8ሁሉም ሰይፍ የታጠቁ፣

ሁሉም በጦርነት የተፈተኑ ናቸው፤

የሌሊት አደጋን ለመከላከልም፣

እያንዳንዳቸው ሰይፋቸውን በወገባቸው ታጥቀዋል።

9ንጉሥ ሰሎሞን የራሱን ሠረገላ ሠራ፤

የሠራውም ከሊባኖስ በመጣ ዕንጨት ነው።

10ምሰሶዎቹን ከብር፣

መደገፊያውንም ከወርቅ ሠራ፤

መቀመጫውም በሐምራዊ ሐር የተሸፈነ ነው፤

ውስጡም በኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፣

አምሮ የተለበጠ ነው።3፥10 ወይም የተለበጠውም ውስጥ፣ ከኢየሩሳሌም ቈነጃጅት የሆነ የፍቅር ስጦታ

11እናንት የጽዮን ቈነጃጅት ውጡ፤

ንጉሥ ሰሎሞን አክሊሉን ደፍቶ እዩት፤

ዘውዱም ልቡ ሐሤት ባደረገባት፣

በዚያች በሰርጉ ዕለት፣

እናቱ የደፋችለት ነው።