مزمور 85 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 85:1-13

الْمَزْمُورُ الْخَامِسُ وَالثَّمَانُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ. مَزْمُورٌ لِبَنِي قُورَحَ

1يَا رَبُّ، قَدْ رَضِيتَ عَنْ أَرْضِكَ، وَأَرْجَعْتَ سَبْيَ يَعْقُوبَ. 2إِذْ غَفَرْتَ لِشَعْبِكَ إِثْمَهُمْ، وَسَتَرْتَ خَطَايَاهُمْ كُلَّهَا. 3سَكَّنْتَ كُلَّ سَخَطِكَ. رَجَعْتَ عَنْ غَضَبِكَ الرَّهِيبِ. 4رُدَّنَا إِلَيْكَ يَا اللهُ مُخَلِّصَنَا، وَاصْرِفْ غَيْظَكَ عَنَّا. 5أَتَسْخَطُ عَلَيْنَا إِلَى الأَبَدِ؟ أَتُطِيلُ غَضَبَكَ مِنْ جِيلٍ إِلَى جِيلٍ؟ 6أَمَا تُحْيِينَا مِنْ جَدِيدٍ فَيَفْرَحَ بِكَ شَعْبُكَ؟ 7أَظْهِرْ لَنَا رَحْمَتَكَ يَا رَبُّ، وَامْنَحْنَا خَلاصَكَ.

8إِنِّي أَسْمَعُ مَا يَتَكَلَّمُ بِهِ اللهُ الرَّبُّ، فَإِنَّهُ يَتَكَلَّمُ بِالسَّلامِ لِشَعْبِهِ وَلأَتْقِيَائِهِ، فَلَا يَرْجِعُونَ إِلَى الْجَهَالَةِ. 9حَقّاً إِنَّ خَلاصَهُ قَرِيبٌ مِنَ الَّذِينَ يَخَافُونَهُ، لِكَيْ يُقِيمَ الْمَجْدُ فِي أَرْضِنَا. 10الرَّحْمَةُ وَالْحَقُّ تَلاقَيَا، الْبِرُّ وَالسَّلامُ تَعَانَقَا. 11يَنْبُتُ الْحَقُّ مِنَ الأَرْضِ، وَيُشْرِفُ الْبِرُّ مِنَ السَّمَاءِ. 12أَيْضاً يُعْطِي الرَّبُّ الْخَيْرَ، فَتُنْتِجُ الأَرْضُ غَلَّاتِهَا الْوَافِرَةَ. 13يَتَقَدَّمُهُ الْبِرُّ، وَيُمَهِّدُ الطَّرِيقَ لِخَطَوَاتِهِ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 85:1-13

መዝሙር 85

ስለ ሰላም የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ለምድርህ በጎ ውለሃል፤

የያዕቆብንም ምርኮ መለስህ።

2የሕዝብህን በደል ይቅር አልህ፤

ኀጢአታቸውንም ሁሉ ሸፈንህ። ሴላ

3መዓትህን ሁሉ አራቅህ፤

ከብርቱ ቍጣህም ተመለስህ።

4መድኀኒታችን የሆንህ አምላክ ሆይ፤ መልሰን፤

በእኛ ላይ የተቃጣውን ቍጣህን መልሰው።

5የምትቈጣን ለዘላለም ነውን?

ቍጣህስ ከትውልድ እስከ ትውልድ ይቀጥላልን?

6ሕዝብህ በአንተ ሐሤት ያደርግ ዘንድ፣

መልሰህ ሕያዋን አታደርገንምን?

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህን አሳየን፤

ማዳንህን ለግሰን።

8እግዚአብሔር አምላክ የሚናገረውን እሰማለሁ፤

ለሕዝቡ፣ ለቅዱሳኑ ሰላምን ይናገራልና፤

ዳሩ ግን ወደ ከንቱ ምግባራቸው አይመለሱ።

9ክብሩ በምድራችን ይኖር ዘንድ፣

ማዳኑ ለሚፈሩት በርግጥ ቅርብ ነው።

10ምሕረትና ታማኝነት ተገናኙ፤

ጽድቅና ሰላም ተቃቀፉ።

11ታማኝነት ከምድር በቀለች፤

ጽድቅም ከሰማይ ተመለከተች።

12እግዚአብሔር በጎ ነገር ይለግሳል፤ ምድራችንም ፍሬዋን ትሰጣለች።

13ጽድቅ በፊቱ ይሄዳል፤

ለአረማመዱም መንገድ ያዘጋጃል።