مراثي إرميا 5 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مراثي إرميا 5:1-22

1اذْكُرْ يَا رَبُّ مَا أَصَابَنَا. انْظُرْ وَعَايِنْ عَارَنَا. 2قَدْ تَحَوَّلَ مِيرَاثُنَا إِلَى الْغُرَبَاءِ وَبُيُوتُنَا إِلَى الأَجَانِبِ. 3أَصْبَحْنَا أَيْتَاماً لَا أَبَ لَنَا، وَأُمَّهَاتُنَا كَالأَرَامِلِ. 4بِالْفِضَّةِ شَرِبْنَا مَاءَنَا. وَبِثَمَنٍ ابْتَعْنَا حَطَبَنَا. 5دَاسَ مُضْطَهِدُونَا أَعْنَاقَنَا، أَعْيَيْنَا وَلَمْ نَجِدْ رَاحَةً. 6خَضَعْنَا بَاسِطِينَ أَيْدِينَا إِلَى أَشُّورَ وَمِصْرَ لِنَشْبَعَ خُبْزاً. 7قَدْ أَخْطَأَ آبَاؤُنَا، وَتَوَارَوْا عَنِ الْوُجُودِ، وَنَحْنُ نَتَحَمَّلُ عِقَابَ آثَامِهِمْ. 8تَسَلَّطَ عَلَيْنَا عَبِيدٌ، وَلَيْسَ مَنْ يُنْقِذُنَا مِنْ أَيْدِيهِمْ. 9بِأَنْفُسِنَا نَأْتِي بِخُبْزِنَا مُجَازِفِينَ بِحَيَاتِنَا مِنْ جَرَّاءِ السَّيْفِ الْكَامِنِ لَنَا فِي الصَّحْرَاءِ. 10جِلْدُنَا مُلْتَهِبٌ كَتَنُّورٍ مِنْ نِيرَانِ الْجُوعِ الْمُحْرِقَةِ. 11اغْتَصَبُوا النِّسَاءَ فِي صِهْيَوْنَ وَالْعَذَارَى فِي مُدُنِ يَهُوذَا. 12عُلِّقَ النُّبَلاءُ بِأَيْدِيهِمْ وَلَمْ يُوَقِّرُوا الشُّيُوخَ. 13سَخَّرُوا الشُّبَّانَ لِلطَّحْنِ، وَهَوَى الصِّبْيَانُ تَحْتَ الْحَطَبِ. 14هَجَرَ الشُّيُوخُ بَوَّابَةَ الْمَدِينَةِ، وَكَفَّ الشُّبَّانُ عَنْ غِنَائِهِمْ. 15انْقَطَعَ فَرَحُ قَلْبِنَا وَتَحَوَّلَ رَقْصُنَا إِلَى نَوْحٍ. 16تَهَاوَى إِكْلِيلُ رَأْسِنَا، فَوَيْلٌ لَنَا لأَنَّنَا قَدْ أَخْطَأْنَا. 17لِهَذَا غُشِيَ عَلَى قُلُوبِنَا، وَأَظْلَمَتْ عُيُونُنَا. 18لأَنَّ جَبَلَ صِهْيَوْنَ أَضْحَى أَطْلالاً تَرْتَعُ فِيهِ الثَّعَالِبُ.

19أَمَّا أَنْتَ يَا رَبُّ، فَتَمْلِكُ إِلَى الأَبَدِ، وَعَرْشُكَ ثَابِتٌ مِنْ جِيلٍ إِلَى جِيلٍ. 20لِمَاذَا تَنْسَانَا إِلَى الأَبَدِ وَتَتْرُكُنَا طُولَ الأَيَّامِ؟ 21رُدَّنَا يَا رَبُّ إِلَيْكَ فَنَرْجِعَ. جِدِّدْ أَيَّامَنَا كَمَا فِي الْعُهُودِ السَّالِفَةِ. 22إِلا إِنْ كُنْتَ قَدْ رَفَضْتَنَا كُلَّ الرَّفْضِ وَغَضِبْتَ عَلَيْنَا أَشَدَّ الْغَضَبِ.

New Amharic Standard Version

ሰቈቃወ 5:1-22

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በእኛ ላይ የደረሰውን ዐስብ፤

ውርደታችንን እይ፤ ተመልከትም።

2ርስታችን ለመጻተኞች፣

ቤቶቻችን ለባዕዳን ዐልፈው ተሰጡ።

3ወላጅ አልባና አባት የሌላቸው ሆንን፤

እናቶቻችን እንደ መበለቶች ሆኑ።

4ለምንጠጣው ውሃ መክፈል ነበረብን፤

ዕንጨታችንንም የምናገኘው በግዢ ነበር።

5የሚያሳድዱን ከተረከዞቻችን ሥር ናቸው፤

ተጨንቀናል ዕረፍትም ዐጥተናል።

6እንጀራ እንጠግብ ዘንድ፣

ለአሦርና ለግብፅ እጃችንን ሰጠን።

7አባቶቻችን ኀጢአት ሠርተው ዐለፉ፤

እኛም የእነርሱን ቅጣት ተሸከምን።

8ባሮች ሠልጥነውብናል፤

ከእጃቸው ነጻ የሚያወጣን ማንም የለም።

9በምድረ በዳ ካለው ሰይፍ የተነሣ፣

በሕይወታችን ተወራርደን እንጀራ አገኘን።

10ቈዳችን እንደ ምድጃ ጠቍሯል፤

በራብም ተቃጥሏል።

11ሴቶች በጽዮን፣

ደናግል በይሁዳ ከተሞች ተደፈሩ።

12መሳፍንት በእነርሱ እጅ ተሰቀሉ፤

ሽማግሌዎችም አልተከበሩም።

13ጕልማሶች ወፍጮ እንዲፈጩ ተገደዱ፤

ወንዶች ልጆች በዕንጨት ሸክም ተንገዳገዱ።

14ሽማግሌዎች ከከተማዪቱ በር ሄደዋል፤

ጕልማሶች ዝማሬያቸውን አቁመዋል።

15ደስታ ከልባችን ጠፍቷል፤

ጭፈራችን ወደ ልቅሶ ተለውጧል።

16አክሊላችን ከራሳችን ላይ ወድቋል፤

ወዮልን፤ ኀጢአት ሠርተናልና!

17ከዚህ የተነሣ ልባችን ደከመ፤

ከእነዚህ የተነሣም ዐይናችን ፈዘዘ፤

18ባዶዋን የቀረችው የጽዮን ተራራ፣

የቀበሮዎች መፈንጫ ሆናለችና።

19አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ለዘላለም ትገዛለህ፤

ዙፋንህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል።

20ስለ ምን ፈጽመህ ትረሳናለህ?

ስለምንስ ለረዥም ጊዜ ትተወናለህ?

21እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ መልሰን፤ እኛም እንመለሳለን፤

ዘመናችንን እንደ ቀድሞው አድስ፤

22ፈጽመህ ካልጣልኸን፣

ከመጠን በላይ ካልተቈጣኸን።