1ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሠራው ሥራ ሁሉ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ አባቱ ዳዊት የቀደሰውን ብሩንና ወርቁን፣ ዕቃዎቹንም ሁሉ አምጥቶ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ግምጃ ቤት አኖራቸው።
ታቦቱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ
5፥2–6፥11 ተጓ ምብ – 1ነገ 8፥1-21
2ከዚያ በኋላ ሰሎሞን የእግዚአብሔርን የኪዳን ታቦት ከዳዊት ከተማ ከጽዮን እንዲያመጡ፣ የእስራኤልን ሽማግሌዎች፣ የየነገዱን መሪዎች ሁሉና የእስራኤላውያንን የቤተ ሰብ አለቆች በኢየሩሳሌም ሰበሰበ። 3የእስራኤልም ሰዎች ሁሉ የሰባተኛው ወር በዓል በሚከበርበት ጊዜ፣ በንጉሡ ፊት ተሰበሰቡ።
4የእስራኤል ሽማግሌዎች በተሰበሰቡም ጊዜ ሌዋውያኑ ታቦቱን አነሡት፤ 5ታቦቱን፣ የመገናኛ ድንኳኑንና በውስጡ ያሉትን የተቀደሱ ዕቃዎች ሁሉ ይዘው ወደ ላይ ወጡ፤ ሌዋውያን የሆኑ ካህናትም ተሸከሟቸው። 6ንጉሥ ሰሎሞንና በአጠገቡ የተሰበሰበው መላው የእስራኤል ጉባኤ ስፍር ቍጥር የሌላቸውን በጎችና በሬዎች በታቦቱ ፊት ሠዉ።
7ካህናቱም የእግዚአብሔርን የኪዳኑን ታቦት የቤተ መቅደሱ ውስጠኛ ክፍል ወደ ሆነው ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ አግብተው ከኪሩቤል ክንፍ በታች ባለው ስፍራው አኖሩት። 8ኪሩቤልም ክንፎቻቸውን ከታቦቱ በላይ ባለው ስፍራ ላይ ዘርግተው፣ ታቦቱንና መሎጊያዎቹን ሸፈኑ። 9መሎጊያዎቹም በጣም ረጃጅም ከመሆናቸው የተነሣ፣ ታቦቱ እስካለበት ድረስ ያሉት ጫፎቻቸው ከቅድስተ ቅዱሳኑ ፊት ለፊት ይታዩ ነበር፤ ከመቅደሱ ውጭ ግን አይታዩም ነበር፤ ዛሬም እዚያው ቦታ ይገኛሉ። 10እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ በኋላ እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ኪዳን ባደረገ ጊዜ፣ ሙሴ በኮሬብ ተራራ በውስጡ ካስቀመጣቸው ከሁለቱ ጽላቶች በቀር በታቦቱ ውስጥ ምንም አልነበረም። 11ካህናቱም ከቤተ መቅደሱ ወጡ፤ እዚያ የነበሩት ካህናት በምድባቸው መሠረት ባይሆንም፣ ሁሉም ራሳቸውን ቀድሰው ነበር። 12መዘምራን የነበሩት ሌዋውያን ሁሉ፣ አሳፍ፣ ኤማን፣ ሄማንና ኤዶታም፣ ወንዶች ልጆቻቸውና የሥጋ ዘመዶቻቸው ሁሉ ያማረ ቀጭን በፍታ ለብሰው፣ ከመሠዊያው በስተ ምሥራቅ በኩል ቆመው ጸናጽል ይጸነጽሉ፣ በገና ይደረድሩና መሰንቆ ይመቱ ነበር፤ እነርሱም መለከት በሚነፉ አንድ መቶ ሃያ ካህናት ታጅበው ነበር። 13መለከት ነፊዎችና ዘማሪዎችም በአንድነት አንድ ድምፅ ሆነው ለእግዚአብሔር ውዳሴና ምስጋና አቀረቡ፤ በመለከት፣ በጸናጽልና በሌሎች መሣሪያዎች ታጅበውም ድምፃቸውን ከፍ በማድረግ እግዚአብሔርን እያወደሱ፣
“እርሱ ቸር ነው፣
ፍቅሩም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”
እያሉ ዘመሩ።
ከዚያም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በደመና ተሞላ። 14የእግዚአብሔር ክብር የአምላክን ቤተ መቅደስ ሞልቶት ስለ ነበር፣ ከደመናው የተነሣ ካህናቱ አገልግሎታቸውን ማከናወን አልቻሉም።
1وقتی كارهای خانهٔ خداوند تمام شد، سليمان، طلا و نقره و تمام ظرفهايی را كه پدرش داوود وقف خانهٔ خدا كرده بود به خزانهٔ خانهٔ خدا آورد.
صندوق عهد به خانهٔ خدا منتقل میشود
(اول پادشاهان 8:1-9)
2آنگاه سليمان پادشاه، تمام سران قبايل و طوايف قوم اسرائيل را به اورشليم دعوت كرد تا صندوق عهد خداوند را كه در صهيون، شهر داوود بود به خانهٔ خدا بياورند. 3همهٔ آنها در روزهای عيد خيمهها در ماه هفتم در اورشليم جمع شدند. 4-5آنگاه كاهنان و لاويان صندوق عهد و خيمهٔ عبادت را با تمام ظروف مقدسی كه در آن بود، به خانهٔ خدا آوردند. 6آنگاه سليمان پادشاه و تمام بنیاسرائيل در برابر صندوق عهد خداوند جمع شدند و آنقدر گاو و گوسفند قربانی كردند كه نمیشد حساب كرد!
7سپس كاهنان، صندوق عهد را به درون قدسالاقداس خانهٔ خداوند بردند و آن را زير بالهای مجسمهٔ فرشتهها قرار دادند. 8مجسمهٔ فرشتهها طوری ساخته شده بود كه بالهايشان روی صندوق عهد خداوند و روی چوبهای حامل صندوق پهن میشد و آن را میپوشاند. 9چوبهای حامل آنقدر دراز بودند كه از داخل اتاق دوم يعنی قدس ديده میشدند، اما از حياط ديده نمیشدند. (اين چوبها هنوز هم در آنجا هستند.) 10در صندوق عهد چيزی جز دو لوح سنگی نبود. وقتی خداوند با قوم خود، پس از بيرون آمدن از مصر، در كوه حوريب عهد و پيمان بست، موسی آن دو لوح را در صندوق عهد گذاشت.
حضور پرجلال خداوند
11در آن روز، تمام كاهنان بدون توجه به نوبت خدمتشان، خود را تقديس5:11 تقديس يعنی جدا کردن، اختصاص دادن و مقدس ساختن. كردند. هنگامی كه كاهنان از قدس بيرون میآمدند 12دستهٔ سرايندگان لاوی به خواندن سرود پرداختند. سرايندگان عبارت بودند از: آساف، هيمان، يدوتون و تمام پسران و برادران ايشان كه لباس كتان بر تن داشتند و در سمت شرقی قربانگاه ايستاده بودند. صد و بيست نفر از كاهنان با نوای شيپور، و لاويان با سنج، عود و بربط، دستهٔ سرايندگان را همراهی میكردند. 13-14دستهٔ سرايندگان به همراهی نوازندگان شيپور، سنج و سازهای ديگر، خداوند را حمد و سپاس میگفتند. سرودی كه میخواندند اين بود: «خداوند نيكوست و محبتش بیپايان!»
در همان وقت، ناگهان ابری خانهٔ خداوند را پوشاند و حضور پرجلال خداوند آن مكان را فرا گرفت، به طوری كه كاهنان نتوانستند به خدمت خود ادامه دهند.