2 ዜና መዋዕል 24 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 24:1-27

ኢዮአስ ቤተ መቅደሱን ማደሱ

24፥1-14 ተጓ ምብ – 2ነገ 12፥1-16

24፥23-27 ተጓ ምብ – 2ነገ 12፥17-21

1ኢዮአስ በነገሠ ጊዜ፣ ዕድሜው ሰባት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም አርባ ዓመት ገዛ። እናቱ ሳብያ የተባለች የቤርሳቤህ ሴት ነበረች። 2ካህኑ ዮዳሄ በሕይወት በነበረበት ዘመን ሁሉ፣ ኢዮአስ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነገር አደረገ። 3ዮዳሄ ሁለት ሚስቶች መረጠለት፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆችም ወለደ።

4ከጥቂት ጊዜ በኋላ ኢዮአስ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለማደስ ወሰነ። 5ካህናቱንና ሌዋውያኑን ሰብስቦም፣ “ወደ ይሁዳ ከተሞች ሄዳችሁ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በየዓመቱ ለማደስ ገንዘብ ከእስራኤል ሁሉ ሰብስቡ፤ ይህንም አሁኑኑ አድርጉት” አላቸው። ሌዋውያኑ ግን ቸል አሉ።

6ስለዚህ ንጉሡ ሊቀ ካህኑን ዮዳሄን ጠርቶ፣ “የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴና የእስራኤል ጉባኤ ለምስክሩ ድንኳን እንዲወጣ የወሰኑትን ግብር ከይሁዳና ከኢየሩሳሌም እንዲያመጡ ሌዋውያኑን ያላተጋሃቸው ለምንድን ነው?” አለው።

7በዚህ ጊዜ የዚያች ክፉ የጎቶልያ ልጆች የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ሰብረው በመግባት የተቀደሱ ዕቃዎች እንኳ ሳይቀሩ፣ ለበኣል ጣዖታት አገልግሎት እንዲውሉ አድርገው ነበር።

8በንጉሡም ትእዛዝ የገንዘብ መሰብሰቢያ ሣጥን ሠርተው በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መግቢያ በር አጠገብ በውጭ በኩል አኖሩት። 9ከዚህ በኋላ እስራኤል በምድረ በዳ ሳሉ የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ያዘዘውን ግብር ለእግዚአብሔር እንዲያመጡ በይሁዳና በኢየሩሳሌም ዐዋጅ ተነገረ። 10ሹማምቱ ሁሉ፣ ሕዝቡም ሁሉ ግብሩን በደስታ አመጡ፤ እስኪሞላም ድረስ በሣጥኑ ውስጥ ጨመሩ። 11ሣጥኑ በሌዋውያኑ እጅ ወደ ንጉሡ ሹማምት በሚደርስበት ጊዜ፣ እነርሱም በውስጡ ብዙ ገንዘብ መኖሩን በሚያዩበት ጊዜ ሁሉ፣ የቤተ መንግሥቱ ጸሓፊና የሊቀ ካህናቱ ሹም ይመጡና ሣጥኑን አጋብተው ወደ ቦታው ይመልሱት ነበር። ይህን በየቀኑ በማድረግ እጅግ ብዙ ገንዘብ ሰበሰቡ። 12ንጉሡና ዮዳሄም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ሥራ እንዲያሠሩ ለተመደቡት ሰዎች ገንዘቡን አስረከቧቸው፤ እነርሱም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለማደስ ድንጋይ ጠራቢዎችንና ዐናጢዎችን እንዲሁም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለመጠገን የብረትና የናስ ሠራተኞችን ቀጠሩ።

13በሥራው ላይ የተሰማሩት ሰዎች ትጉሃን ስለ ነበሩ፣ ሥራው በእጃቸው ተከናወነ፤ የእግዚአብሔርንም ቤተ መቅደስ ቀደም ሲል በነበረው ዐይነት ዐደሱት፤ አጠናከሩትም። 14ከጨረሱም በኋላ ቀሪውን ገንዘብ ወደ ንጉሡና ወደ ዮዳሄ አመጡ፤ በገንዘቡም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ዕቃዎች ማለትም ለአገልግሎትና ለሚቃጠል መሥዋዕት የሚውሉ ዕቃዎች እንደዚሁም ጭልፋዎችና ሌሎች የወርቅና የብር ዕቃዎችም ተሠሩ። ዮዳሄ በሕይወት በነበረበት ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሚቃጠል መሥዋዕት ዘወትር ይቀርብ ነበር።

15ዮዳሄ ሸምግሎ ዕድሜ ከጠገበ በኋላ፣ በመቶ ሠላሳ ዓመቱ ሞተ። 16እርሱም በእስራኤል ውስጥ ለእግዚአብሔርና ለቤተ መቅደሱ መልካም ሠርቷልና በዳዊት ከተማ በነገሥታቱ መቃብር ተቀበረ።

የኢዮአስ ክፋት

17ከዮዳሄ ሞት በኋላ የይሁዳ ሹማምት መጥተው ለንጉሡ ታማኝነታቸውን ገለጡ፤ ንጉሡም አደመጣቸው። 18እነርሱም የአባቶቻቸውን አምላክ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ትተው፣ የአሼራን ዐምዶችና ጣዖታትን አመለኩ፤ በበደላቸውም ምክንያት የእግዚአብሔር ቍጣ በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ መጣ። 19ወደ እግዚአብሔር ይመልሷቸው ዘንድ እርሱ ነቢያቱን ወደ ሕዝቡ ሰደደ፤ ነቢያቱም መሰከሩባቸው፤ እነርሱ ግን አላዳመጡም።

20የእግዚአብሔርም መንፈስ በካህኑ በዮዳሄ ልጅ በዘካርያስ ላይ መጣ፤ እርሱም በሕዝቡ ፊት ቆሞ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ለምን ትተላለፋላችሁ? አይሳካላችሁም፤ እናንተ እግዚአብሔርን ስለ ተዋችሁት እርሱም ትቷችኋል” አላቸው።

21እነርሱ ግን አሤሩበት፤ በንጉሡም ትእዛዝ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አደባባይ ላይ በድንጋይ ወግረው ገደሉት።

22ንጉሥ ኢዮአስ የዘካርያስ አባት ዮዳሄ ያደረገለትን ቸርነት አላሰበም፤ በዚህ ፈንታ ልጁን ገደለው፤ በሚሞትበትም ጊዜ፣ “እግዚአብሔር ይየው፤ እርሱው ይበቀልህ” አለ።

23በዓመቱም መጨረሻ24፥23 ምናልባት መስከረም፣ ጥቅምትና ኅዳር፣ የሶርያ ሰራዊት በኢዮአስ ላይ ዘመተ፤ ይሁዳንና ኢየሩሳሌምንም ወርሮ የሕዝቡን መሪዎች ሁሉ ደመሰሰ፤ ምርኮውንም ሁሉ ወደ ንጉሡ ወደ ደማስቆ ላከ። 24የሶርያ ሰራዊት ሰዎች ጥቂት ቢሆኑም እንኳ እግዚአብሔር በጣም የሚበልጠውን ሰራዊት በእጃቸው አሳልፎ ሰጠ፤ ይሁዳ የአባቶቹን አምላክ እግዚአብሔርን ስለ ተወ፣ በኢዮአስ ላይ ተፈረደበት። 25ሶርያውያንም በወጡ ጊዜ ኢዮአስን ክፉኛ አቍስለው፣ ጥለውት ሄዱ፤ የካህኑን የዮዳሄን ልጅ ስለ ገደለም፣ ሹማምቱ አሢረውበት በዐልጋው ላይ እንዳለ ገደሉት። በዚህ ሁኔታም ሞቶ በዳዊት ከተማ ተቀበረ እንጂ በነገሥታቱ መቃብር አልተቀበረም።

26በእርሱ ላይ ያሤሩትም የአሞናዊቱ የሰምዓት ልጅ ዛባድና የሞዓባዊቱ የሰማሪት ልጅ ዮዛባት ነበሩ። 27የወንዶች ልጆቹ ታሪክ፣ ስለ እርሱ የተነገሩት ብዙ ትንቢቶችና የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መታደስ በነገሥታቱ የታሪክ መዛግብት ተጽፈዋል። ልጁ አሜስያስም በእርሱ ፈንታ ነገሠ።

Thai New Contemporary Bible

2พงศาวดาร 24:1-27

โยอาชทรงซ่อมแซมพระวิหาร

(2พกษ.12:1-21)

1เมื่อโยอาชขึ้นเป็นกษัตริย์ พระองค์ทรงมีพระชนมายุเจ็ดพรรษา และทรงครองราชย์อยู่ในกรุงเยรูซาเล็มสี่สิบปี ราชมารดาคือศิบียาห์จากเบเออร์เชบา 2โยอาชทรงทำสิ่งที่ถูกต้องในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้าตลอดชั่วอายุของปุโรหิตเยโฮยาดา 3เยโฮยาดาหามเหสีให้สององค์และโยอาชทรงมีโอรสธิดาหลายองค์

4ต่อมาโยอาชตั้งพระทัยจะซ่อมแซมพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 5จึงทรงเรียกปุโรหิตและคนเลวีมาประชุม แล้วตรัสกับพวกเขาว่า “จงไปยังหัวเมืองต่างๆ ของยูดาห์ และรวบรวมเงินประจำปีจากอิสราเอลทั้งปวง เพื่อการซ่อมแซมพระวิหารของพระเจ้าของท่าน จงลงมือทำเดี๋ยวนี้” แต่คนเลวีไม่ได้ทำตามทันที

6ฉะนั้นกษัตริย์ทรงเรียกเยโฮยาดาหัวหน้าปุโรหิตมาถามว่า “ทำไมท่านจึงไม่ออกคำสั่งให้คนเลวีออกไปเก็บภาษีบำรุงพระวิหารจากหัวเมืองต่างๆ ของยูดาห์และกรุงเยรูซาเล็ม? โมเสสผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้ากำหนดให้เก็บภาษีนี้จากประชากรอิสราเอลเพื่อบำรุงรักษาเต็นท์แห่งพันธสัญญา”

7ก่อนหน้านี้บริวารของพระนางอาธาลิยาห์ผู้ชั่วร้ายได้บุกเข้าไปในพระวิหาร และถึงกับนำของศักดิ์สิทธิ์ไปใช้สำหรับพระบาอัล

8โยอาชตรัสสั่งให้ทำหีบใบหนึ่งตั้งไว้ข้างนอกที่ประตูพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 9และออกหมายประกาศในยูดาห์และในกรุงเยรูซาเล็ม ให้ประชาชนนำภาษีซึ่งโมเสสผู้รับใช้ของพระเจ้าได้กำหนดให้เก็บจากชนอิสราเอลในถิ่นกันดารมาถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า 10เจ้าหน้าที่และประชากรทั้งปวงต่างยินดีนำเงินมาใส่ไว้ในหีบจนเต็ม 11เมื่อใดที่คนเลวียกหีบมาพบเจ้าหน้าที่ของกษัตริย์และพวกเขาเห็นว่ามีเงินมาก ราชเลขากับเจ้าหน้าที่ของมหาปุโรหิตจะเก็บเงินออกจากหีบ แล้วนำหีบไปตั้งไว้ที่เดิม พวกเขาทำเช่นนี้สม่ำเสมอจนได้เงินก้อนใหญ่ 12กษัตริย์และเยโฮยาดามอบเงินนั้นแก่ผู้ควบคุมการก่อสร้างพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า คนเหล่านี้จ้างช่างก่อ ช่างไม้ ช่างเหล็ก และช่างทองสัมฤทธิ์มาซ่อมแซมพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า

13เจ้าหน้าที่ฝ่ายต่างๆ ปฏิบัติงานอย่างขยันขันแข็ง ดูแลให้งานซ่อมแซมคืบหน้าไป พวกเขาปฏิสังขรณ์พระวิหารตามรูปแบบเดิมและเสริมให้แข็งแกร่งขึ้น 14เมื่อทุกอย่างเสร็จสิ้น พวกเขานำเงินที่เหลือมามอบแด่กษัตริย์และเยโฮยาดา และใช้ทำเครื่องใช้ไม้สอยต่างๆ สำหรับพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า เครื่องใช้ในพิธีและการถวายเครื่องเผาบูชา รวมทั้งชามและภาชนะเงินและทอง มีการถวายเครื่องเผาบูชาในพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าอย่างสม่ำเสมอตลอดชั่วอายุของปุโรหิตเยโฮยาดา

15เยโฮยาดามีอายุยืนมาก เขาสิ้นชีวิตเมื่ออายุ 130 ปี 16เขาถูกฝังไว้รวมกับกษัตริย์องค์ต่างๆ ในเมืองดาวิด เพราะเขาได้บำเพ็ญประโยชน์มากมายในอิสราเอลเพื่อพระเจ้าและเพื่อพระวิหารของพระองค์

ความชั่วร้ายของโยอาช

17หลังจากเยโฮยาดาสิ้นชีวิต บรรดาเจ้าหน้าที่ของยูดาห์มาถวายบังคมกษัตริย์และพระองค์ทรงฟังพวกเขา 18พวกเขาพากันละทิ้งพระวิหารของพระยาห์เวห์พระเจ้าของบรรพบุรุษไปกราบไหว้เสาเจ้าแม่อาเชราห์และรูปเคารพต่างๆ พระพิโรธของพระเจ้าจึงตกแก่ยูดาห์และเยรูซาเล็มเนื่องจากความผิดของพวกเขา 19แม้องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงใช้ผู้เผยพระวจนะมาเพื่อนำพวกเขาหันกลับไปหาพระองค์ และถึงแม้ว่าผู้เผยพระวจนะเหล่านั้นว่ากล่าวตักเตือน แต่พวกเขาก็ไม่ยอมฟัง

20แล้วพระวิญญาณของพระเจ้าเสด็จลงมาเหนือเศคาริยาห์บุตรปุโรหิตเยโฮยาดา เขายืนอยู่ต่อหน้าประชาชนและกล่าวว่า “พระเจ้าตรัสว่า ‘เหตุใดพวกเจ้าไม่เชื่อฟังพระบัญชาขององค์พระผู้เป็นเจ้า? พวกเจ้าจะไม่เจริญเพราะเจ้าได้ละทิ้งองค์พระผู้เป็นเจ้าพระองค์จึงได้ทรงละทิ้งเจ้า’ ”

21แต่พวกเขาคบคิดกันกำจัดเศคาริยาห์ พวกเขารุมเอาหินขว้างเศคาริยาห์จนตายในลานพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าตามพระราชโองการของกษัตริย์ 22กษัตริย์โยอาชไม่ได้ระลึกถึงบุญคุณของเยโฮยาดาบิดาของเศคาริยาห์เลย แต่กลับฆ่าลูกของเขา ขณะจะสิ้นชีวิต เศคาริยาห์กล่าวว่า “ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทอดพระเนตรสิ่งนี้และเรียกร้องความรับผิดชอบจากท่าน”

23ในปีต่อมา24:23 คงจะเป็นฤดูใบไม้ผลิกองทัพอารัมมารบกับโยอาช บุกโจมตียูดาห์และเยรูซาเล็ม สังหารผู้นำทุกคนของประชาชนและนำของที่ยึดมาได้ทั้งหมดกลับไปถวายกษัตริย์ของพวกเขาในเมืองดามัสกัส 24แม้กองทัพอารัมมีกำลังพลน้อย แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าก็ทรงให้พวกเขาชนะกองทัพใหญ่ เพราะยูดาห์ได้ละทิ้งพระยาห์เวห์พระเจ้าของบรรพบุรุษ โยอาชจึงถูกลงโทษ 25เมื่อชาวอารัมกลับไป ทิ้งให้โยอาชบาดเจ็บสาหัส ข้าราชการของพระองค์คบคิดกันกำจัดโยอาชที่ได้ประหารบุตรของปุโรหิตเยโฮยาดา จึงปลงพระชนม์โยอาชซึ่งบรรทมอยู่บนแท่น แล้วฝังพระศพไว้ในเมืองดาวิด แต่ไม่ใช่ในสุสานหลวง

26ผู้สมคบกันคือศาบาด24:26 เป็นอีกรูปหนึ่งของโยศาบาดบุตรนางชิเมอัทชาวอัมโมน และเยโฮซาบาดบุตรนางชิมริท24:26 เป็นอีกรูปหนึ่งของโชเมอร์ชาวโมอับ 27เรื่องราวเกี่ยวกับโอรสของโยอาช คำพยากรณ์ต่างๆ ว่าด้วยโยอาช และเรื่องราวการซ่อมแซมพระวิหารมีบันทึกไว้ในจดหมายเหตุกษัตริย์องค์ต่างๆ แล้วอามาซิยาห์โอรสของพระองค์ขึ้นครองราชย์แทน