2 ዜና መዋዕል 20 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 20:1-37

ኢዮሣፍጥ ሞዓብንና አሞንን ድል ማድረጉ

1ከዚህ በኋላ ሞዓባውያንና አሞናውያን ከጥቂት ምዑናውያን20፥1 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን ዕብራይስጡ ምድያማውያን ይላል። ጋር ሆነው ኢዮሣፍጥን ለመውጋት መጡ።

2ሰዎችም መጥተው ኢዮሣፍጥን፣ “ግዙፍ ሰራዊት ሊወጋህ ከሙት20፥2 አንድ የዕብራይስጥ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን አራም ይላል። ባሕር ወዲያ ካለው ከኤዶም20፥2 ምንም እንኳ የሙት ባሕር መሆኑን ግልጽ ቢሆንም አንዳንድ ቅጆች ሙት የሚለውን ቃል አይጨምሩም። መጥቶብሃል፤ እነሆም፣ ሐሴሶን ታማር በተባለው በዓይንጋዲ ናቸው” አሉት። 3ኢዮሣፍጥም እጅግ ስለ ፈራ እግዚአብሔርን ለመፈለግ ፊቱን አቀና፤ በይሁዳም ሁሉ ጾም ዐወጀ። 4የይሁዳ ሕዝብም የእግዚአብሔርን ርዳታ ይሻ ዘንድ በአንድነት ተሰበሰበ፤ ከይሁዳ ከተሞች ሁሉም እግዚአብሔርን ለመፈለግ መጡ። 5ኢዮሣፍጥም በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ፣ ከአዲሱ አደባባይ ፊት ለፊት በይሁዳና በኢየሩሳሌም ጉባኤ መካከል ቆመ፤ 6እንዲህም አለ፤

“የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በሰማይ የምትኖር አምላክ አይደለህምን? የምድር ሕዝቦችን መንግሥታት ሁሉ የምትገዛ አንተ ነህ፤ ኀይልና ሥልጣን በእጅህ ነው፤ ሊቋቋምህም የሚችል ማንም የለም። 7አምላካችን ሆይ፤ የዚህችን ምድር ነዋሪዎች ከሕዝብህ ከእስራኤል ፊት አሳድደህ ያስወጣህና ለወዳጅህ ለአብርሃም ዘሮች ለዘላለም የሰጠሃቸው አንተ አይደለህምን? 8እነርሱም ተቀመጡባት፤ ለስምህ መቅደስ ሠሩባት፤ እንዲህም አሉ፤ 9‘የፍርድ ሰይፍም ሆነ የቸነፈር ወይም የራብ መከራ ቢደርስብን፣ ስምህ በተጠራበት በዚህ ቤተ መቅደስ ፊት ለፊት፣ በፊትህ ቆመን በጭንቀታችን ወደ አንተ እንጮሃለን፤ አንተም ትሰማናለህ፤ ታድነናለህም።’

10“እስራኤል ከግብፅ በወጡ ጊዜ፣ ግዛታቸውን እንዳይወርሩባቸው በማድረግህ ከእነርሱ ተመልሰው ሳያጠፏቸው የቀሩት የአሞን፣ የሞዓብና የሴይር ተራራ ሰዎች እነሆ እዚህ አሉ። 11እነሆ፣ አንተ ርስት አድርገህ ከሰጠኸን ምድር እኛን በማፈናቀል ወሮታ ሊመልሱልን መጥተዋል። 12አምላካችን ሆይ፤ አንተ አትፈርድባቸውምን? የመጣብንን ይህን ታላቅ ሰራዊት እንቋቋም ዘንድ ዐቅም የለንምና የምናደርገውን አናውቅም፤ ነገር ግን ዐይኖቻችን ወዳንተ ናቸው።”

13የይሁዳ ሰዎች ሁሉ ከሚስቶቻቸው፣ ከልጆቻቸውና ከሕፃኖቻቸው ጋር በእግዚአብሔር ፊት ቆመው ነበር።

14በዚህ ጊዜ የአሳፍ ዘር በሆነው በሌዋዊው በዘካርያስ ልጅ፣ በየሕዚኤል ላይ የእግዚአብሔር መንፈስ መጣ። ዘካርያስም የበናያስ ልጅ ሲሆን፣ በናያስም የማታን ልጅ የሆነው የይዒኤል ልጅ ነው።

15እርሱም እንዲህ አለ፤ “ንጉሥ ኢዮሣፍጥ፣ እናንተም በይሁዳና በኢየሩሳሌም የምትኖሩ ሁሉ አድምጡ! እግዚአብሔር እንዲህ ይላችኋል፤ ‘ውጊያው የእግዚአብሔር እንጂ የእናንተ አይደለምና፣ ከዚህ ታላቅ ሰራዊት የተነሣ አትፍሩ፣ አትደንግጡ፣ 16ነገ በእነርሱ ላይ ውረዱ፤ እነርሱ በጺጽ መተላለፊያ ሽቅብ ይወጣሉ፣ እናንተም በይሩኤል ምድረ በዳ ውስጥ በሸለቆው መጨረሻ ላይ ታገኟቸዋላችሁ። 17ይህን ጦርነት የምትዋጉት እናንተ አይደላችሁም፤ ይሁዳና ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ቦታ ቦታችሁን ያዙ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ እግዚአብሔር የሚሰጣችሁንም ማዳን እዩ። አትፍሩ፤ አትደንግጡም፤ ነገውኑ ውጡና ግጠሟቸው፤ እግዚአብሔርም ከእናንተ ጋር ይሆናል።’ ”

18ኢዮሣፍጥ በግንባሩ ወደ መሬት ተደፋ፤ የይሁዳና የኢየሩሳሌምም ሕዝብ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ወደቁ፤ ሰገዱም። 19ከቀዓትና ከቆሬ ወገኖች ጥቂት ሌዋውያንም ቆመው፣ እጅግ ከፍ ባለ ድምፅ የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

20በማግስቱም ጧት በማለዳ ተነሥተው ወደ ቴቁሔ ምድረ በዳ ሄዱ። መንገድ እንደ ጀመሩም ኢዮሣፍጥ ቆሞ፣ “ይሁዳና የኢየሩሳሌም ሕዝብ ሆይ፣ አድምጡኝ! በአምላካችሁ በእግዚአብሔር እመኑ፤ ትጸኑማላችሁ። በነቢያቱም እመኑ፤ ይሳካላችሁማል” አላቸው። 21ከሕዝቡም ጋር ከተመካከረ በኋላ ከሰራዊቱ ፊት ቀድመው በመሄድ፣

እግዚአብሔርን አመስግኑ፣

ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራልና”

እያሉ ለእግዚአብሔር የሚዘምሩና ስለ ቅድስናውም ክብር የሚያወድሱ ሰዎችን መደበ።

22መዘመርና ማወደስ እንደ ጀመሩም፣ እግዚአብሔር ይሁዳን በወረሩት በአሞን፣ በሞዓብና በሴይር ተራራ ሰዎች ላይ ድብቅ ጦር አመጣባቸው፤ ተሸነፉም። 23የአሞንና የሞዓብ ሰዎችም የሴይርን ተራራ ሰዎች ለማጥፋትና ለመደምሰስ ተነሡባቸው። ከሴይር የመጡትን ሰዎች ካጠፉ በኋላም፣ እርስ በርስ ተጠፋፉ።

24የይሁዳ ሰዎች ምድረ በዳውን ቍልቍል ወደሚያሳየው ቦታ መጥተው ግዙፉን ሰራዊት ሲመለከቱ፣ መሬቱ ሬሳ በሬሳ ሆኖ አዩ፤ አንድም ሰው አላመለጠም። 25ኢዮሣፍጥና ሰዎቹም ምርኳቸውን ለማጋዝ ሄዱ፤ በዚያም መካከል እጅግ ብዙ መሣሪያና ልብስ፣20፥25 አንዳንድ የዕብራይስጥና የቩልጌት ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ሬሳ ይላል። ሊሸከሙ ከሚችሉትም በላይ ውድ ዕቃዎችን አገኙ። ምርኮውም ከመብዛቱ የተነሣ ለመሰብሰብ ሦስት ቀን ፈጀ። 26በአራተኛውም ቀን እግዚአብሔርን ባመሰገኑበት በበረከት20፥26 በዕብራይስጡ፣ በራካ ማለት በረከት ማለት ነው። ሸለቆ ተሰበሰቡ፤ ያም ስፍራ እስከ ዛሬ ድረስ የበረከት ሸለቆ ተብሎ የተጠራው ከዚህ የተነሣ ነው።

27እግዚአብሔር በጠላቶቻቸው ላይ እንዲደሰቱ ስላደረጋቸው፣ የይሁዳና የኢየሩሳሌም ሰዎች ሁሉ በኢዮሣፍጥ እየተመሩ፣ በታላቅ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። 28ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ እንደ ገቡም በበገና፣ በመሰንቆና በመለከት ድምፅ ታጅበው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አመሩ።

29እግዚአብሔር የእስራኤልን ጠላቶች እንዴት እንደ ተዋጋቸው በሰሙ መንግሥታት ሁሉ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ፍርሀት ወደቀባቸው።

30አምላኩ በየአቅጣጫው ዕረፍት ስለ ሰጠው፣ የኢዮሣፍጥ መንግሥት ሰላም አግኝቶ ነበር።

የኢዮሣፍጥ ዘመነ መንግሥት ፍጻሜ

20፥31–21፥1 ተጓ ምብ – 1ነገ 22፥41-50

31ኢዮሣፍጥ በይሁዳ ላይ ነገሠ። መንገሥ በጀመረ ጊዜም ዕድሜው ሠላሳ አምስት ዓመት ሲሆን፣ በኢየሩሳሌም ተቀሞጦ ሃያ አምስት ዓመት ገዛ። እናቱም የሺልሒ ልጅ ዓዙባ ነበረች። 32እርሱም በአባቱ በአሳ መንገድ ሄደ፤ ከዚያም ፈቀቅ አላለም፤ በእግዚአብሔርም ፊት መልካም የሆነውን ነገር አደረገ። 33ያም ሆኖ ግን ማምለኪያ ኰረብታዎች ሙሉ በሙሉ አልተወገዱም፤ ሕዝቡም ገና ልቡን በአባቶቹ አምላክ ላይ አልጣለም ነበር።

34በኢዮሣፍጥ ዘመነ መንግሥት ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ የተከናወኑት ሌሎች ተግባራት የአናኒ ልጅ ኢዩ በዘገበው የእስራኤል ነገሥታት የታሪክ መጽሐፍ ተመዝግቧል።

35ከዚህ በኋላ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ ሥራው እጅግ ክፉ ከሆነው ከእስራኤል ንጉሥ ከአካዝያስ ጋር የስምምነት ውል አደረገ፤ 36የንግድ መርከብ20፥36 ዕብራይስጡ፣ ወደ ተርሴስ ሊሄዱ የሚችሉ መርከቦች ይላል። ለመሥራትም ተስማሙ፤ መርከቦቹንም በዔጽዮንጋብር አሠሩ። 37የመሪሳ ሰው የሆነው የዶዳያ ልጅ አልዓዛር በኢዮሣፍጥ ላይ፣ “ከአካዝያስ ጋር የስምምነት ውል ስለ አደረግህ፣ እግዚአብሔር ሥራህን ያፈርሰዋል” ሲል ትንቢት ተናገረበት፤ መርከቦቹም ተሰበሩ፤ ለንግዱም ሥራ መንቀሳቀስ አልቻሉም።20፥37 ዕብራይስጡ፣ ወደ ተርሴስ መሄድ አልቻሉም ይላል።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

历代志下 20:1-37

约沙法祷告退敌

1后来摩押人、亚扪人同一些米乌尼20:1 米乌尼人”出现在古希腊译本,但希伯来文是“亚扪人”。一起来攻打约沙法2有人禀告约沙法说:“有一支大军从死海对岸的以东20:2 以东”希伯来文是“亚兰”。杀来,已经攻到哈洗逊·他玛。”哈洗逊·他玛就是隐·基底3约沙法很害怕,决定寻求耶和华,在整个犹大宣告禁食。 4犹大人聚集起来寻求耶和华。他们从犹大各城前来寻求耶和华。

5约沙法站在耶和华殿的新院里,在犹大耶路撒冷的民众面前, 6说:“我们祖先的上帝耶和华啊,你不是住在天上的上帝吗?你主宰万邦万国,你手中有权柄和能力,无人能抵挡你。 7我们的上帝啊,你不是曾经在你的以色列子民面前驱逐这地方的居民,把这片土地赐给你的朋友亚伯拉罕的后裔永远作产业吗? 8你的子民在这里居住,为你的名建造殿宇,说, 9‘如果我们遭遇祸患,无论是战祸、瘟疫或饥荒,当我们在急难中站在这殿前向你呼求时,你必定垂听,施行拯救,因为你的名在这殿里。’

10“从前以色列人离开埃及的时候,你不准他们侵犯亚扪人、摩押人和来自西珥山的人,他们就绕道而行,没有毁灭这些人。 11但现在这些人要报复我们,把我们从你赐给我们作产业的地方赶走。 12我们的上帝啊,难道你不惩罚他们吗?面对前来攻击的大军,我们无力抵挡,不知道该怎么办,我们只有仰望你。”

13犹大人与他们的妻子、儿女和婴孩都站在耶和华面前。 14这时,耶和华的灵降在雅哈悉身上。雅哈悉利未亚萨的后裔、玛探雅的玄孙、耶利的曾孙、比拿雅的孙子、撒迦利雅的儿子。 15他说:“全体犹大人、耶路撒冷的居民和约沙法王啊,你们要留心听!耶和华对你们如此说,‘你们不要因敌军强大而恐惧惊慌,因为战争的胜败不在乎你们,而在乎上帝。 16明天你们下去迎敌,敌军会从洗斯坡上来,你们一定会在耶鲁伊勒旷野前面的谷口遇见他们。 17你们不用与他们交战,只要守住阵势,站立不动,看耶和华为你们施行拯救。犹大人和耶路撒冷人啊,不要恐惧,不要惊慌,明天只管出去迎敌,耶和华必与你们同在!’”

18于是,约沙法面伏于地,所有犹大人和耶路撒冷的居民也都俯伏在耶和华面前敬拜祂。 19哥辖族和可拉族的利未人都站起来,高声赞美以色列的上帝耶和华。 20第二天清晨,众人起来去提哥亚的旷野。他们出发的时候,约沙法站着说:“犹大人和耶路撒冷的居民啊,请听我说!要信靠你们的上帝耶和华,你们就必坚立;要相信祂的先知,你们就必得胜。” 21约沙法与众人商议后,就派歌乐手穿上圣洁的礼服走在军队前面,赞美耶和华,说:“你们要称谢耶和华,因祂的慈爱永远长存!”

22他们开始唱歌赞美的时候,耶和华就派伏兵击杀前来攻打犹大亚扪人、摩押人和来自西珥山的人,打败了他们。 23原来亚扪人和摩押人攻击来自西珥山的人,消灭了他们,然后亚扪人和摩押人又自相残杀。

24犹大人来到旷野的瞭望塔俯瞰那支大军,发现敌军尸横遍野,无一幸免。 25约沙法和他的百姓前去拾财物,发现尸体中有许多财物、衣服和贵重物品,多得拿不完。他们拾了三天才拾完。 26第四天,他们聚集到一个山谷,一起称颂耶和华。那里从此名叫比拉迦20:26 比拉迦”就是称赞的意思。 谷,直到今天。

27犹大人和耶路撒冷人在约沙法的带领下,欢欢喜喜地返回耶路撒冷,因为耶和华使他们战胜了仇敌。 28他们一路弹琴、鼓瑟、吹号回到耶路撒冷,进入耶和华的殿。 29列邦列国听闻耶和华打败了以色列的敌人,都很惧怕。 30因此,约沙法执政期间国家太平,因为他的上帝赐他四境平安。

约沙法逝世

31约沙法三十五岁登基做犹大王,在耶路撒冷执政二十五年。他母亲叫阿苏巴,是示利希的女儿。 32约沙法效法他父亲亚撒,做耶和华视为正的事,不偏不离。 33然而,他没有拆除丘坛,民众还没有全心归向他们祖先的上帝。

34约沙法其他的事迹自始至终都记在哈拿尼的儿子耶户的史记上。耶户的史记收录在以色列的列王史上。

35后来,犹大约沙法与作恶多端的以色列亚哈谢修好。 36他们在以旬·迦别造船,要去他施37玛利沙多大瓦的儿子以利以谢约沙法预言说:“因为你与亚哈谢修好,耶和华必破坏你所造的船只。”那些船只果然坏了,无法前往他施