2 ዜና መዋዕል 12 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 12:1-16

ሺሻቅ በኢየሩሳሌም ላይ ዘመተ

12፥9-16 ተጓ ምብ – 1ነገ 14፥2125-31

1ሮብዓም መንግሥቱን ከመሠረተና ካጸና በኋላ፣ እርሱና እስራኤል12፥1 በዜና መዋዕል ካልዕ መጽሐፍ ተደጋግሞ እንደ ተጠቀሰው ይህ ይሁዳ ነው። ሁሉ የእግዚአብሔርን ሕግ ተዉ። 2እግዚአብሔርን ከመበደላቸው የተነሣም፣ ሮብዓም በነገሠ በአምስተኛው ዓመት የግብፅ ንጉሥ ሺሻቅ በኢየሩሳሌም ላይ ዘመተ። 3ከግብፅ አብረውት የመጡትን ዐሥራ ሁለት ሺሕ ሠረገላዎች፣ ስድሳ ሺሕ ፈረሰኞችና ስፍር ቍጥር የሌላቸውን የሊቢያ፣ የሱኪምና የኢትዮጵያ ወታደሮችን ይዞ፣ 4የተመሸጉትን የይሁዳ ከተሞች በቍጥጥሩ ሥር በማድረግ እስከ ኢየሩሳሌም ዘለቀ።

5ከዚህ በኋላ ነቢዩ ሸማያ ወደ ሮብዓምና ሺሻቅን ፈርተው በኢየሩሳሌም ወደ ተሰበሰቡት ወደ እስራኤል መሪዎች መጥቶ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እናንተ ትታችሁኛል፤ ስለዚህ እኔም በሺሻቅ እጅ ትቼአችኋለሁ’ ” አላቸው።

6የእስራኤል መሪዎችና ንጉሡ ራሳቸውን በማዋረድ፣ “እግዚአብሔር ጻድቅ ነው” አሉ።

7እግዚአብሔርም ራሳቸውን እንዳዋረዱ ባየ ጊዜ፣ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ ሸማያ መጣ፤ “ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ስላዋረዱ እታደጋቸዋለሁ እንጂ አላጠፋቸውም፤ ቍጣዬም በሺሻቅ እጅ በኢየሩሳሌም ላይ አይፈስስም። 8ይሁን እንጂ እኔን በማገልገልና የሌሎችን አገሮች ነገሥታት በማገልገል መካከል ያለውን ልዩነት ያውቁ ዘንድ፣ ለእርሱ ይገዛሉ።”

9የግብፅ ንጉሥ ሺሻቅ ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ፣ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ንብረትና የቤተ መንግሥቱን ንብረት ዘርፎ ወሰደ፤ ሰሎሞን ያሠራው የወርቅ ጋሻ ሳይቀር፣ እንዳለ ሁሉንም አጋዘው። 10ንጉሥ ሮብዓምም በተወሰዱት ፈንታ የናስ ጋሻዎች ሠርቶ፤ የቤተ መንግሥቱን ቅጥር በሮች ለሚጠብቁ የዘብ አለቆች በኀላፊነት ሰጠ። 11ንጉሡ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በሚሄድበት ጊዜ ሁሉ፣ ዘበኞቹ ጋሻዎቹን አንግበው ያጅቡት ነበር፤ ከዚያም በኋላ ጋሻዎቹን ወደ ዘበኞች ክፍል ይመልሱ ነበር።

12ሮብዓም ራሱን ዝቅ አድርጎ ስላዋረደ፣ የእግዚአብሔር ቍጣ ከእርሱ ተመለሰ፤ ፈጽሞም አላጠፋውም። በይሁዳም ደግሞ በጥቂቱም ቢሆን መልካም ነገር ተገኝቶ ነበር።

13ንጉሥ ሮብዓም በሚገባ ተደላድሎ በኢየሩሳሌም በንጉሥነቱ ቀጠለ፣ ሲነግሥ ዕድሜው አርባ አንድ ዓመት ነበር፤ እግዚአብሔር ስሙን በዚያ ለማኖር ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ በመረጣት በኢየሩሳሌም ከተማ ተቀምጦም፣ ዐሥራ ሰባት ዓመት ገዛ፤ እናቱም ናዕማ የምትባል አሞናዊት ነበረች። 14እግዚአብሔርን ይሻ ዘንድ ልቡን ስላላዘጋጀ ክፉ ነገር አደረገ።

15ሮብዓም በዘመነ መንግሥቱ ያከናወናቸው ተግባሮች ሁሉ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ድረስ ነቢዩ ሸማያ በጻፈው የታሪክ መዝገብና ባለ ራእዩ አዶ በዘገበው የትውልድ ሐረግ ታሪክ የሚገኝ አይደለምን? በሮብዓምና በኢዮርብዓም መካከል የማያቋርጥ ጦርነት ነበር። 16ሮብዓም እንደ አባቶቹ ሁሉ አንቀላፋ፤ በዳዊትም ከተማ ተቀበረ፤ ልጁ አብያም በእርሱ ፈንታ ነገሠ።

New International Reader’s Version

2 Chronicles 12:1-16

Shishak Attacks Jerusalem

1Rehoboam had made his position as king secure. He had become very strong. Then he turned away from the law of the Lord. So did all the people of Judah. 2They hadn’t been faithful to the Lord. So Shishak attacked Jerusalem. It was in the fifth year that Rehoboam was king. Shishak was king of Egypt. 3He came with 1,200 chariots and 60,000 horsemen. Troops of Libyans, Sukkites and Cushites came with him from Egypt. There were so many of them they couldn’t be counted. 4Shishak captured the cities of Judah that had high walls around them. He came all the way to Jerusalem.

5Then Shemaiah the prophet came to Rehoboam and the leaders of Judah. They had gathered together in Jerusalem. They were afraid of Shishak. Shemaiah said to them, “The Lord says, ‘You have left me. So now I am leaving you to Shishak.’ ”

6The king and the leaders of Israel made themselves humble in the Lord’s sight. They said, “The Lord does what is right and fair.”

7The Lord saw they had made themselves humble. So he gave a message to Shemaiah. The Lord said, “They have made themselves humble in my sight. So I will not destroy them. Instead, I will soon save them. Even though I am very angry with Jerusalem, I will not use Shishak to destroy them. 8But the people of Jerusalem will be brought under his control. Then they will learn the difference between serving me and serving the kings of other lands.”

9Shishak, the king of Egypt, attacked Jerusalem. He carried away the treasures of the Lord’s temple. He also carried the treasures of the royal palace away. He took everything. That included the gold shields Solomon had made. 10So King Rehoboam made bronze shields to take their place. He gave them to the commanders of the guards who were on duty at the entrance to the royal palace. 11Every time the king went to the Lord’s temple, the guards went with him. They carried the shields. Later, they took them back to the room where they were kept.

12Rehoboam had made himself humble in the Lord’s sight. So the Lord turned his anger away from him. Rehoboam wasn’t totally destroyed. In fact, some good things happened in Judah.

13King Rehoboam had made his position secure in Jerusalem. He continued as king. He was 41 years old when he became king. He ruled for 17 years in Jerusalem. It was the city the Lord had chosen out of all the cities in the tribes of Israel. He wanted to put his Name there. The name of Rehoboam’s mother was Naamah from Ammon. 14Rehoboam did what was evil. That’s because he hadn’t worshiped the Lord with all his heart.

15The events of Rehoboam’s rule from beginning to end are written down. They are written in the records of Shemaiah and Iddo, the prophets. The records deal with family histories. Rehoboam and Jeroboam were always at war with each other. 16Rehoboam joined the members of his family who had already died. He was buried in the City of David. Rehoboam’s son Abijah became the next king after him.