2 ዜና መዋዕል 12 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 12:1-16

ሺሻቅ በኢየሩሳሌም ላይ ዘመተ

12፥9-16 ተጓ ምብ – 1ነገ 14፥2125-31

1ሮብዓም መንግሥቱን ከመሠረተና ካጸና በኋላ፣ እርሱና እስራኤል12፥1 በዜና መዋዕል ካልዕ መጽሐፍ ተደጋግሞ እንደ ተጠቀሰው ይህ ይሁዳ ነው። ሁሉ የእግዚአብሔርን ሕግ ተዉ። 2እግዚአብሔርን ከመበደላቸው የተነሣም፣ ሮብዓም በነገሠ በአምስተኛው ዓመት የግብፅ ንጉሥ ሺሻቅ በኢየሩሳሌም ላይ ዘመተ። 3ከግብፅ አብረውት የመጡትን ዐሥራ ሁለት ሺሕ ሠረገላዎች፣ ስድሳ ሺሕ ፈረሰኞችና ስፍር ቍጥር የሌላቸውን የሊቢያ፣ የሱኪምና የኢትዮጵያ ወታደሮችን ይዞ፣ 4የተመሸጉትን የይሁዳ ከተሞች በቍጥጥሩ ሥር በማድረግ እስከ ኢየሩሳሌም ዘለቀ።

5ከዚህ በኋላ ነቢዩ ሸማያ ወደ ሮብዓምና ሺሻቅን ፈርተው በኢየሩሳሌም ወደ ተሰበሰቡት ወደ እስራኤል መሪዎች መጥቶ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እናንተ ትታችሁኛል፤ ስለዚህ እኔም በሺሻቅ እጅ ትቼአችኋለሁ’ ” አላቸው።

6የእስራኤል መሪዎችና ንጉሡ ራሳቸውን በማዋረድ፣ “እግዚአብሔር ጻድቅ ነው” አሉ።

7እግዚአብሔርም ራሳቸውን እንዳዋረዱ ባየ ጊዜ፣ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ ሸማያ መጣ፤ “ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ስላዋረዱ እታደጋቸዋለሁ እንጂ አላጠፋቸውም፤ ቍጣዬም በሺሻቅ እጅ በኢየሩሳሌም ላይ አይፈስስም። 8ይሁን እንጂ እኔን በማገልገልና የሌሎችን አገሮች ነገሥታት በማገልገል መካከል ያለውን ልዩነት ያውቁ ዘንድ፣ ለእርሱ ይገዛሉ።”

9የግብፅ ንጉሥ ሺሻቅ ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ፣ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ንብረትና የቤተ መንግሥቱን ንብረት ዘርፎ ወሰደ፤ ሰሎሞን ያሠራው የወርቅ ጋሻ ሳይቀር፣ እንዳለ ሁሉንም አጋዘው። 10ንጉሥ ሮብዓምም በተወሰዱት ፈንታ የናስ ጋሻዎች ሠርቶ፤ የቤተ መንግሥቱን ቅጥር በሮች ለሚጠብቁ የዘብ አለቆች በኀላፊነት ሰጠ። 11ንጉሡ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በሚሄድበት ጊዜ ሁሉ፣ ዘበኞቹ ጋሻዎቹን አንግበው ያጅቡት ነበር፤ ከዚያም በኋላ ጋሻዎቹን ወደ ዘበኞች ክፍል ይመልሱ ነበር።

12ሮብዓም ራሱን ዝቅ አድርጎ ስላዋረደ፣ የእግዚአብሔር ቍጣ ከእርሱ ተመለሰ፤ ፈጽሞም አላጠፋውም። በይሁዳም ደግሞ በጥቂቱም ቢሆን መልካም ነገር ተገኝቶ ነበር።

13ንጉሥ ሮብዓም በሚገባ ተደላድሎ በኢየሩሳሌም በንጉሥነቱ ቀጠለ፣ ሲነግሥ ዕድሜው አርባ አንድ ዓመት ነበር፤ እግዚአብሔር ስሙን በዚያ ለማኖር ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ በመረጣት በኢየሩሳሌም ከተማ ተቀምጦም፣ ዐሥራ ሰባት ዓመት ገዛ፤ እናቱም ናዕማ የምትባል አሞናዊት ነበረች። 14እግዚአብሔርን ይሻ ዘንድ ልቡን ስላላዘጋጀ ክፉ ነገር አደረገ።

15ሮብዓም በዘመነ መንግሥቱ ያከናወናቸው ተግባሮች ሁሉ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ድረስ ነቢዩ ሸማያ በጻፈው የታሪክ መዝገብና ባለ ራእዩ አዶ በዘገበው የትውልድ ሐረግ ታሪክ የሚገኝ አይደለምን? በሮብዓምና በኢዮርብዓም መካከል የማያቋርጥ ጦርነት ነበር። 16ሮብዓም እንደ አባቶቹ ሁሉ አንቀላፋ፤ በዳዊትም ከተማ ተቀበረ፤ ልጁ አብያም በእርሱ ፈንታ ነገሠ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歷代志下 12:1-16

埃及侵犯猶大

1羅波安王位穩定、國勢強盛後,就離棄耶和華的律法,以色列人也都隨從他。 2羅波安王執政第五年,埃及示撒上來攻打耶路撒冷,因為猶大君民對耶和華不忠。 3示撒率領一千二百輛戰車、六萬騎兵及無數的路比人、蘇基人和古實人。 4他攻陷了猶大的堅城,直逼耶路撒冷

5那時,猶大各首領因為戰事都聚集在耶路撒冷示瑪雅先知去見羅波安和眾首領,對他們說:「耶和華說,『你們背棄了我,所以我也要離棄你們,把你們交在示撒手中。』」 6王與以色列的眾首領聽了,就謙卑下來說:「耶和華是公義的。」 7耶和華見他們謙卑下來,就對示瑪雅說:「既然他們謙卑下來,我就不滅絕他們,給他們留一條生路。我也不會藉示撒耶路撒冷傾倒我的憤怒。 8然而,他們必做示撒的僕人,好讓他們體驗事奉我和服侍世上的君王的不同。」

9埃及示撒帶兵攻陷了耶路撒冷,把耶和華殿裡和王宮裡的財寶及所羅門造的金盾牌擄掠一空。 10羅波安王就造了銅盾牌代替金盾牌,交給看守宮門的護衛長看管。 11每次王進耶和華的殿,護衛兵就帶上盾牌,用完後放回護衛房。 12王謙卑下來後,耶和華便不再向他發怒,沒有將他完全毀滅。況且,在猶大還有一些善事。

羅波安逝世

13羅波安王在耶路撒冷鞏固了自己的勢力,繼續做王。他四十一歲登基,在耶路撒冷執政十七年。耶和華從以色列眾支派中選擇耶路撒冷作為立祂名的城。羅波安的母親叫拿瑪,是亞捫人。 14羅波安行為邪惡,因為他不專心尋求耶和華。

15他執政期間的事件自始至終都記在示瑪雅先知和易多先見的史記上。羅波安耶羅波安之間常有爭戰。 16羅波安與祖先同眠後,葬在大衛城。他兒子亞比雅繼位。