2 ነገሥት 5 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 5:1-27

ንዕማን ከለምጽ ተፈወሰ

1በዚህ ጊዜ ንዕማን የሶርያ ንጉሥ ጦር አዛዥ ነበረ፤ እግዚአብሔር በዚህ ሰው አማካይነት፣ ሶርያ ድልን እንድትጐናጸፍ ስላደረጋት በጌታው ዘንድ ታላቅና የተከበረ ሰው ነበር። ጀግና ወታደር ቢሆንም ለምጽ5፥1 በዚህ ስፍራ እንዲሁም በቍጥር 3፡6፡7፡11 እና 12 ላይ የዕብራይስጡ ቃል ቈዳን የሚያጠቁ በሽታዎች ሁሉ የሚያሳይ ነው። ወጥቶበት ነበር።

2አደጋ ጣዮች ከሶርያ ወጥተው፣ ከእስራኤል ምድር አንዲት ልጃገረድ ማረኩ፤ እርሷም የንዕማንን ሚስት ታገለግላት ነበር። 3እመቤቷንም፣ “ጌታዬ በሰማርያ ያለውን ነቢይ ሄዶ ቢያገኘው እኮ ከዚህ ለምጹ ይፈውሰው ነበር” አለቻት።

4ንዕማንም ወደ ጌታው ሄዶ ከእስራኤል የመጣችው ልጃገረድ ያለችውን ነገረው። 5የሶርያም ንጉሥ፣ “በል እንግዲያው አሁኑኑ ሂድ፤ እኔም ለእስራኤል ንጉሥ ደብዳቤ እጽፋለሁ” አለው፤ ስለዚህ ንዕማን ዐሥር መክሊት5፥5 340 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብር፣ ስድስት ሺሕ ሰቅል5፥5 70 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ወርቅና ዐሥር ሙሉ ልብስ ይዞ ሄደ። 6ለእስራኤልም ንጉሥ የያዘው ደብዳቤ፣ “ከለምጹ እንድትፈውሰው ይህን ደብዳቤ አስይዤ አገልጋዬን ንዕማንን ወደ አንተ ልኬዋለሁ” የሚል ነው።

7የእስራኤልም ንጉሥ ደብዳቤውን ወዲያው እንዳነበበ ልብሱን ቀድዶ፣ “ከለምጽ እንድፈውሰው ይህን ሰው ወደ እኔ መላኩ እኔ ገድዬ ማዳን የምችል አምላክ ሆኜ ነውን? እንግዲህ ጠብ ሲፈልገኝ እዩ!” አለ።

8የእግዚአብሔር ሰው ኤልሳዕ፣ የእስራኤል ንጉሥ ልብሱን መቅደዱን በሰማ ጊዜ፣ እንዲህ ሲል ላከበት፤ “ልብስህን ለምን ቀደድህ? ሰውየው ወደ እኔ ይምጣ፤ ከዚያም በእስራኤል ነቢይ መኖሩን ያውቃል።” 9ስለዚህ ንዕማን በፈረሶቹና በሠረገሎቹ ሆኖ በኤልሳዕ ቤት ደጃፍ ሲደርስ ቆመ። 10ኤልሳዕም፣ “ሂድና በዮርዳኖስ ሰባት ጊዜ ታጠብ፤ ሥጋህ ይፈወሳል፤ አንተም ትነጻለህ” ብሎ እንዲነግረው መልእክተኛ ላከበት።

11ንዕማን ግን ተቈጥቶ እንዲህ በማለት ሄደ፤ “እኔ እኮ በርግጥ ወደ እኔ መጥቶ በመቆም የአምላኩን የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ፣ በእጁም ዳስሶ ከለምጽ በሽታዬ የሚፈውሰኝ መስሎኝ ነበር። 12ለዚህ ለዚህ የደማስቆ ወንዞች አባናና ፋርፋር ከየትኞቹም የእስራኤል ውሆች አይሻሉምን? ለመታጠብ ለመታጠብማ በእነርሱ ታጥቤ መንጻት አልችልምን?” ስለዚህ በቍጣ ተመለሰ።

13የንዕማን አገልጋዮች ግን ወደ እርሱ ቀርበው፣ “አባት ሆይ፤ ነቢዩ ከዚህ ከበድ ያለ ነገር እንድታደርግ ቢነግርህ ኖሮ አታደርገውም ነበርን? ታዲያ፣ ‘ታጠብና ንጻ’ ቢልህ ምኑ አስቸገረህ?” አሉት። 14ስለዚህ ንዕማን ወረደ፤ የእግዚአብሔር ሰው እንደ ነገረውም በዮርዳኖስ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ አለ፤ ሥጋውም እንደ ትንሽ ልጅ ሥጋ ሆነ፤ ነጻም።

15ከዚያም ንዕማን ከጭፍሮቹ ሁሉ ጋር ወደ እግዚአብሔር ሰው ተመልሶ ሄደ፤ በፊቱም ቆሞ፣ “እነሆ በእስራኤል አገር እንጂ በዓለም ሁሉ ሌላ አምላክ አለመኖሩን ተረድቻለሁ፤ ስለዚህ አሁንም ከአገልጋይህ ስጦታ እንድትቀበል እለምንሃለሁ” አለው። 16ነቢዩም፣ “የማገለግለውን ሕያው እግዚአብሔርን፣ ምንም ነገር አልቀበልም” ሲል መለሰ። ምንም እንኳ ንዕማን አስጨንቆ ቢለምነውም አልተቀበለም። 17ንዕማንም እንዲህ አለው፤ “ስጦታውን የማትቀበል ከሆነ፣ ከእግዚአብሔር በቀር ለማንኛውም አምላክ የሚቃጠል ወይም ሌላ መሥዋዕት ስለማላቀርብ፣ ሁለት የበቅሎ ጭነት ዐፈር እንድወስድ ትፈቅድልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ። 18ነገር ግን እግዚአብሔር ስለ አንድ ነገር ብቻ አገልጋይህን ይቅር ይበለው፤ ይኸውም ጌታዬ ለመስገድ ወደ ሬሞን ቤተ ጣዖት በሚገባበት ጊዜ ክንዴን ሲደገፍ እኔም እንደ እርሱ በዚያ ብሰግድ፣ በሬሞን ቤተ ጣዖት በመስገዴ እግዚአብሔር አገልጋይህን ይቅር ይበለው።”

19ኤልሳዕም፣ “በሰላም ሂድ” አለው። ንዕማን ጥቂት ራቅ ብሎ እንደ ሄደ፣ 20የእግዚአብሔር ሰው አገልጋይ ግያዝ፣ “ጌታዬ፤ ይህ ሶርያዊ ንዕማን ያመጣውን አለመቀበሉ ደግም አይደል፤ ሕያው እግዚአብሔርን! ተከትዬ ሄጄ ከእርሱ አንድ ነገር ማግኘት አለብኝ” ብሎ ዐሰበ።

21ስለዚህ ግያዝ ንዕማንን ተከተለው፤ ንዕማንም ግያዝ እየሮጠ ወደ እርሱ መምጣቱን ባየ ጊዜ፣ ሊገናኘው ከሠረገላው ወርዶ፣ “ምነው፤ በደኅና መጣህን?” ሲል ጠየቀው።

22ግያዝም፣ “ሁሉም ደኅና ነው፤ ግን ጌታዬ፣ ‘ከነቢያት ማኅበር ሁለት ወጣቶች ከኰረብታማው አገር ከኤፍሬም ወደ እኔ አሁን በድንገት ስለ መጡ፣ እባክህ፤ አንድ መክሊት5፥22 34 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብርና ሁለት ሙሉ ልብስ ስጣቸው ብለህ ንገር’ ብሎ ልኮኛል” አለው።

23ንዕማንም፣ “እባክህ፤ ሁለት መክሊት ውሰድ” በማለት ግያዝን አስጨንቆ ለመነው። ከዚያም ሁለቱን መክሊት ብር፣ በሁለት ከረጢት ውስጥ አስሮ ሁለት ሙሉ ልብስ ጨምሮ ለሁለት አገልጋዮቹ አስያዘ፤ እነርሱም ያን ተሸክመው ከግያዝ ፊት ፊት ሄዱ። 24ግያዝም ወደ ኰረብታው እንደ ደረሰ፣ ዕቃዎቹን ከአገልጋዮቹ ተቀብሎ በቤቱ ውስጥ አስቀመጠ፤ ሰዎቹንም አሰናብቷቸው ሄዱ። 25ከዚያም ገብቶ በጌታው በኤልሳዕ ፊት ቆመ።

ኤልሳዕም፣ “ግያዝ ሆይ፤ የት ነበርህ?” ሲል ጠየቀው።

ግያዝም፣ “አገልጋይህ የትም አልሄደም” ብሎ መለሰ።

26ኤልሳዕ ግን እንዲህ አለው፤ “ያ ሰው ሊገናኝህ ከሠረገላው ሲወርድ፣ መንፈሴ ከአንተ ጋር አልሄደምን? እንዲያው ለመሆኑ ጊዜው ገንዘብና ልብስ፣ የወይራ ዘይት ተክልና የወይን ተክል ቦታ፣ የበግና የከብት መንጋ፣ ወንድና ሴት አገልጋይ የሚቀበሉበት ነውን? 27ስለዚህ የንዕማን ለምጽ በአንተ ላይ ይጣበቃል፤ ለዘላለምም ወደ ዘርህ ይተላለፋል።” ከዚያም ግያዝ ከኤልሳዕ ፊት ወጣ፤ እንደ በረዶ እስኪነጣም ድረስ ለምጻም ሆነ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

列王纪下 5:1-27

以利沙医治乃缦

1乃缦亚兰王的元帅,甚得亚兰王器重,因为耶和华借他使亚兰人打了许多胜仗。他是英勇的战士,只是患了麻风病。 2亚兰人袭击以色列时,曾掳回一个以色列少女,这少女做了乃缦妻子的婢女。 3有一天,她对主母说:“要是我主人去见撒玛利亚的那位先知就好了!他一定能治好我主人的麻风病。” 4乃缦把这以色列少女的话告诉亚兰王。 5亚兰王说:“你去吧。我会写信给以色列王的。”于是,乃缦带了三百四十公斤银子、七十公斤金子和十套衣服,启程前往以色列6他带给以色列王的信上写着:“谨以此信介绍我的臣仆乃缦到你那里,你要医好他的麻风病。” 7以色列王读完信后,就撕裂衣服说:“难道我是上帝吗?我能操纵人的生死吗?这人竟叫我医好一个人的麻风病!他只是想找借口攻打我。”

8上帝的仆人以利沙听说以色列王撕裂了衣服,便派人去对王说:“你为什么撕裂衣服呢?让那人到我这里来,我要让他知道以色列有先知。” 9乃缦带领车辆和马匹到了以利沙的家,站在门口。 10以利沙派使者出去对乃缦说:“你到约旦河里洗七次,你的皮肤就会复原,并得到洁净。” 11乃缦却怒冲冲地走了。他说:“我以为他一定会出来见我,为我站着求告他的上帝耶和华,用手在我的患处晃一晃,医好我的麻风病。 12大马士革亚波纳河和法尔法河不比以色列所有的河都好吗?难道我在那里洗就不能得到洁净吗?”于是,他怒冲冲地转身走了。 13他的仆人上前对他说:“我父啊,先知若吩咐你做一件大事,难道你会不去做吗?何况他只是说你去洗洗就可以洁净!” 14乃缦就去约旦河,照上帝仆人的话在河里洗了七次,便洁净了,皮肤变得像小孩子的一样。

15乃缦率领全体随从回到上帝的仆人那里,站在他面前说:“如今我才知道,除了以色列,普天下没有上帝。请你收下仆人的礼物。” 16以利沙说:“我凭我事奉的永活上帝起誓,我决不接受。”乃缦再三请求,他仍不肯接受。 17乃缦说:“如果你不肯接受礼物,请你容许仆人用两头骡子驮些泥土回去。从此以后,我不再献燔祭或平安祭给其他神明,只献给耶和华。 18但有一件事,愿耶和华饶恕仆人。我主人进入临门庙祭拜时,他会扶着我的手,这样我也得随着他弯腰。若我在临门庙里弯腰,愿耶和华饶恕我。” 19以利沙对他说:“你安心地走吧。”

20乃缦刚走不远,上帝仆人以利沙的仆人基哈西心想:“我主人没有收亚兰乃缦带来的礼物就让他走了。我凭永活的耶和华起誓,我一定要追上去,向他要点东西。” 21他便去追赶乃缦乃缦见后面有人赶来,就下车迎接他,问他:“一切都好吗?” 22基哈西答道:“一切都好。我主人派我来告诉你,刚才有两位年轻的先知从以法莲山区来见他,请你赐给他们三十四公斤银子和两套衣服。” 23乃缦说:“请你拿走六十八公斤银子吧!”并再三请他接受,然后把六十八公斤银子装进两个袋子,连同两套衣服,交给他的两个仆人抬走,基哈西跟在他们后面。 24到了山冈,基哈西接过银子和衣服,放进屋里,便让他们回去了。 25基哈西进去侍立在以利沙面前,以利沙问他:“基哈西,你刚才去哪里了?”基哈西答道:“仆人哪里也没有去。” 26以利沙对他说:“那人下车回头迎接你的时候,我的心不也在那里吗?现在岂是接受人家银子、衣服、橄榄园、葡萄园、牛羊和仆婢的时候? 27因此,你和你的后代会永远沾染乃缦的麻风病。”基哈西离开以利沙时,患了麻风病,皮肤像雪一样白。