2 ነገሥት 22 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 22:1-20

የሕጉ መጽሐፍ ተገኘ

22፥1-20 ተጓ ምብ – 2ዜና 34፥1-28-28

1ኢዮስያስ ሲነግሥ ዕድሜው ገና ስምንት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ሠላሳ አንድ ዓመት ገዛ። እናቱም የባሱሮት አገር ሰው የአዳያ ልጅ ይዲዳ ነበረች። 2ኢዮስያስም በእግዚአብሔር ፊት መልካም ነገር አደረገ፤ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አላለም፤ አባቱ ዳዊት በሄደበት መንገድ ሁሉ ሄደ።

3በዘመነ መንግሥቱ በዐሥራ ስምንተኛውም ዓመት ኢዮስያስ የሜሶላምን የልጅ ልጅ የኤዜልያስን ልጅ ጸሓፊውን ሳፋንን ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ላከው፤ እንዲህም አለው፤ 4“ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ኬልቅያስ ውጣ፤ የበር ጠባቂዎች ከሕዝቡ ሰብስበው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የገባው ገንዘብ ምን ያህል እንደ ሆነ ራሱ እንዲቈጥረው አድርግ፤ 5ይህም የቤተ መቅደሱን ሥራ እንዲቈጣጠሩ ለተሾሙት ሰዎች ይሰጥ፤ እነርሱም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለሚያድሱት ይክፈሏቸው፤ 6የሚከፍሉትም ለዐናጺዎች፣ ለግንበኞችና ለድንጋይ ጠራቢዎች ነው። እንዲሁም ለቤተ መቅደሱ እድሳት ሥራ የሚሆኑ ሳንቃዎችና የተጠረቡ ድንጋዮች ይግዙበት። 7ሰዎቹ ታማኞች ስለ ሆኑም የተሰጣቸውን ገንዘብ መቈጣጠር አያስፈልግም።”

8ሊቀ ካህናቱ ኬልቅያስ ጸሓፊውን ሳፋንን፣ “የሕጉን መጽሐፍ እኮ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ አገኘሁት” ብሎ ሰጠው፤ እርሱም ተቀብሎ አነበበው። 9ከዚያም ጸሓፊው ሳፋን ሄዶ ለንጉሡ፣ “ሹማምትህ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ የነበረውን ገንዘብ አውጥተዋል፤ ቤተ መቅደሱን እየተቈጣጠሩ ለሚያሠሩትም አስረክበዋል” አለው። 10ከዚያም ጸሓፊው ሳፋን ለንጉሡ፣ “ሊቀ ካህናቱ ኬልቅያስ መጽሐፍ ሰጥቶኛል” ብሎ ነገረው። ሳፋንም ለንጉሡ ከመጽሐፉ አነበበለት።

11ንጉሡም የሕጉን መጽሐፍ ቃል ሲሰማ ልብሱን ቀደደ። 12ከዚያም ካህኑን ኬልቅያስን፣ የሳፋን ልጅ አኪቃምን፣ የሚክያስን ልጅ ዓክቦርን፣ ጸሓፊውን ሳፋንንና የንጉሡን የቅርብ አገልጋይ ዓሳያን እንዲህ ሲል አዘዛቸው፤ 13“ሂዱና ስለ እኔ፣ ስለ ሕዝቡና ስለ ይሁዳም ሁሉ በተገኘው በዚህ መጽሐፍ የተጻፈው ምን እንደ ሆነ እግዚአብሔርን ጠይቁ፤ ምክንያቱም አባቶቻችን ለዚህ መጽሐፍ ቃል ባለመታዘዛቸው፣ እኛን በተመለከተም በዚሁ ላይ የተጻፈውን ሁሉ ባለመፈጸማቸው፣ በእኛ ላይ የሚነድደው የእግዚአብሔር ቍጣ ታላቅ ነውና።”

14ካህኑ ኬልቅያስ፣ አኪቃም፣ ዓክቦርና፣ ሳፋን፣ ዓሳያም የሐርሐስ የልጅ ልጅ፣ የቲቁዋ ልጅ የአልባሳት ጠባቂውን የሴሌምን ሚስት ነቢዪቱን ሕልዳናን ለመጠየቅ ሄዱ። እርሷም የምትኖረው ኢየሩሳሌም ውስጥ በሁለተኛው ሰፈር ነበር።

15ነቢዪቱም፣ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር የሚለው ይህ ነው፤ ‘ወደ እኔ ለላካችሁ ሰው እንዲህ ብላችሁ ንገሩት፤ 16እግዚአብሔር የሚለው ይህ ነው፤ የይሁዳ ንጉሥ ባነበበው መጽሐፍ የተጻፈውን ሁሉ በዚህ ቦታና በሕዝቡ ላይ አመጣለሁ። 17እኔን ስለተውኝና ለሌሎች አማልክት ዕጣን ስላጠኑ፣ እጆቻቸው በሠሯቸውም አማልክት ሁሉ22፥17 ወይም፣ በሠሩት ሥራ ሁሉ ስላስቈጡኝ፣ ቍጣዬ በዚህ ቦታ ላይ ይነድዳል፤ አይጠፋምም።’ 18እግዚአብሔርን እንድትጠይቁ ወደዚህ ቦታ ለላካችሁ ለይሁዳ ንጉሥ ይህን ንገሩት፤ ስለ ሰማኸው ነገር የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር የሚለው ይህ ነው፤ 19‘ለርግማንና ለጥፋት የተዳረጉ ስለ መሆናቸው በዚህ ቦታና በሕዝቡ ላይ የተናገርኩትን ስትሰማ ልብህ ስለ ተነካና ራስህን በእግዚአብሔር ፊት ስላዋረድህ፣ ልብስህንም ቀድደህ በፊቴ ስላለቀስህ እግዚአብሔር ሰምቼሃለሁ ብሏል። 20ስለዚህ ወደ አባቶችህ እሰበስብሃለሁ፤ ወደ መቃብር በሰላም ትወርዳለህ፤ በዚህ ቦታም የማመጣውን መከራ ሁሉ ዐይኖችህ አያዩም።’ ”

ሰዎቹም መልሱን ለንጉሡ ይዘውለት ሄዱ።

Thai New Contemporary Bible

2พงศ์กษัตริย์ 22:1-20

พบหนังสือธรรมบัญญัติ

(2พศด.34:1-2,8-28)

1เมื่อโยสิยาห์ขึ้นเป็นกษัตริย์ พระองค์ทรงมีพระชนมายุแปดพรรษา ทรงครองราชย์อยู่ในกรุงเยรูซาเล็ม 31 ปี ราชมารดาคือเยดีดาห์ธิดาของอาดายาห์จากโบสคาท 2โยสิยาห์ทรงทำสิ่งที่ถูกต้องในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้าและทรงดำเนินตามแบบอย่างของดาวิดผู้เป็นบรรพบุรุษทุกประการ โดยไม่ได้หันเหไปทางขวาหรือทางซ้าย

3ในปีที่สิบแปดแห่งรัชกาลกษัตริย์โยสิยาห์ พระองค์ทรงใช้ราชเลขาชาฟานบุตรอาซาลิยาห์หลานเมชุลลามไปยังพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 4โยสิยาห์ตรัสสั่งว่า “จงขึ้นไปพบมหาปุโรหิตฮิลคียาห์ บอกให้เขารวบรวมเงินที่ปุโรหิตซึ่งเฝ้าประตูพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าเก็บจากประชาชนที่มานมัสการ 5และนำไปมอบแก่ผู้ที่ได้รับการแต่งตั้งให้บังคับบัญชางานพระวิหาร เพื่อจ่ายให้แก่คนงานที่มาซ่อมแซมพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า 6คือช่างไม้ ช่างก่อสร้าง และช่างก่อ และเพื่อซื้อไม้และหินสกัดที่ใช้ในการซ่อมแซมพระวิหาร 7พวกเขาไม่ต้องทำรายงานการเงินซึ่งพวกเขาได้รับมา เพราะพวกเขาทำงานด้วยความซื่อสัตย์สุจริต”

8มหาปุโรหิตฮิลคียาห์แจ้งราชเลขาชาฟานว่า “ข้าพเจ้าได้พบหนังสือพระบัญญัติในพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า” แล้วเขามอบให้ชาฟานอ่าน 9ราชเลขาชาฟานจึงไปทูลรายงานกษัตริย์ว่า “ข้าราชสำนักได้จ่ายเงินที่มีอยู่ในพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าให้คนงานและผู้ควบคุมการซ่อมแซมพระวิหาร” 10แล้วราชเลขาชาฟานทูลกษัตริย์ว่า “ปุโรหิตฮิลคียาห์ได้มอบหนังสือนี้แก่ข้าพระบาท” ชาฟานจึงอ่านหนังสือนั้นต่อหน้ากษัตริย์

11เมื่อกษัตริย์ได้ทรงฟังเนื้อความในหนังสือบทบัญญัตินั้นก็ทรงฉีกฉลองพระองค์ 12และทรงบัญชาปุโรหิตฮิลคียาห์ อาหิคัมบุตรชาฟาน อัคโบร์บุตรมีคายาห์ ราชเลขาชาฟาน และมหาดเล็กอาสายาห์ว่า 13“จงไปทูลถามองค์พระผู้เป็นเจ้าให้เราและเหล่าประชากรทั่วทั้งยูดาห์เกี่ยวกับสิ่งที่บันทึกไว้ในหนังสือที่ได้พบนี้ พระพิโรธขององค์พระผู้เป็นเจ้าที่เผาผลาญเรานั้นร้ายแรงนัก เพราะบรรพบุรุษของเราไม่ได้ปฏิบัติตามถ้อยคำในหนังสือนี้เลย ซึ่งมีบันทึกเกี่ยวโยงมาถึงเราทั้งหลาย”

14ปุโรหิตฮิลคียาห์ อาหิคัมบุตรชาฟาน อัคโบร์บุตรมีคายาห์ ราชเลขาชาฟาน และมหาดเล็กอาสายาห์ จึงไปพบผู้เผยพระวจนะหญิงฮุลดาห์ซึ่งอาศัยอยู่ที่เยรูซาเล็มแขวงสอง นางเป็นภรรยาของชัลลูมบุตรทิกวาห์ผู้เป็นบุตรของฮารฮัสผู้ดูแลเครื่องทรง

15นางกล่าวกับพวกเขาว่า “พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสดังนี้ว่า จงแจ้งผู้ที่ใช้เจ้ามาหาเราว่า 16องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า เราจะนำหายนะทุกอย่างมายังที่แห่งนี้และมายังประชากรตามที่เขียนไว้ในหนังสือซึ่งกษัตริย์แห่งยูดาห์ได้อ่านนั้น 17เพราะพวกเขาได้ทอดทิ้งเราไปเผาเครื่องหอมถวายเทพเจ้าอื่นๆ และยั่วโทสะของเราด้วยรูปเคารพทั้งปวงที่มือของพวกเขาได้ทำขึ้น22:17 หรือด้วยทุกสิ่งที่พวกเขาได้ทำขึ้น ความโกรธของเราจะเผาผลาญที่แห่งนี้และจะระงับไม่ได้’ 18จงบอกกษัตริย์ยูดาห์ซึ่งใช้พวกเจ้ามาทูลถามองค์พระผู้เป็นเจ้านั้นว่า ‘พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสเกี่ยวกับข้อความที่เจ้าได้ยินดังนี้ว่า 19เนื่องจากจิตใจของเจ้าน้อมรับและเจ้าได้ถ่อมตัวลงต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าเมื่อได้ยินสิ่งที่เรากล่าวไว้เกี่ยวกับสถานที่นี้และประชากรที่ว่าจะถูกสาปแช่งและจะต้องเริศร้าง และเนื่องจากเจ้าได้ฉีกเสื้อผ้าและร่ำไห้ต่อหน้าเรา เราได้ยินแล้ว องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้ 20ฉะนั้นเราจะรวบรวมเจ้าไปอยู่กับบรรพบุรุษและเจ้าจะถูกฝังอย่างสงบสุข ไม่ต้องเห็นหายนะทั้งปวงซึ่งเราจะนำมายังสถานที่นี้’ ”

พวกเขาจึงนำคำตอบของนางกลับไปทูลกษัตริย์โยสิยาห์