2 ነገሥት 16 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 16:1-20

የይሁዳ ንጉሥ አካዝ

16፥1-20 ተጓ ምብ – 2ዜና 28፥1-27

1የሮሜልዩ ልጅ ፋቁሔ በነገሠ በዐሥራ ሰባተኛው ዓመት፣ የይሁዳ ንጉሥ፣ የኢዮአታም ልጅ አካዝ ነገሠ። 2አካዝ ሲነግሥ ዕድሜው ሃያ ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ዐሥራ ስድስት ዓመት ገዛ። አባቱ ዳዊት ያደረገውን መልካም ነገር በአምላኩ በእግዚአብሔር ፊት አላደረገም። 3እርሱም የእስራኤልን ነገሥታት መንገድ ተከተለ፤ ይልቁንም እግዚአብሔር ከእስራኤላውያን ፊት ያሳደዳቸውን የአሕዛብን ርኩሰት ተከትሎ፣ ልጁን በእሳት የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ።16፥3 ወይም፣ ልጁን ገደለ 4እንዲሁም ኰረብታ ላይ ባሉ ማምለኪያ ስፍራዎች፣ በኰረብታ ዐናቶችና ቅጠሉ በተንሰራፋው ዛፍ ሥር ሁሉ ሠዋ፤ ዕጣንም አጤሰ።

5የሶርያ ንጉሥ ረአሶንና የእስራኤል ንጉሥ የሮሜልዩ ልጅ ፋቁሔ ኢየሩሳሌምን ለመውጋትና አካዝን ለመክበብ ወጡ፤ ይሁን እንጂ ሊያሸንፉት አልቻሉም። 6በዚያን ጊዜም የሶርያ ንጉሥ ረአሶን የይሁዳን ሰዎች አሳድዶ፣ ኤላትን ወደ ሶርያ ግዛት መለሰ፤ ከዚያም ኤዶማውያን ወደ ኤላት መጥተው እስከ ዛሬ በዚያ ይኖራሉ።

7ከዚህ የተነሣም አካዝ፣ ወደ አሦር ንጉሥ ወደ ቴልጌልቴልፌልሶር፣ “እኔ አገልጋይህም ልጅህም ነኝ፤ ስለዚህ መጥተህ ከሚወጉኝ ከሶርያ ንጉሥና ከእስራኤል ንጉሥ እጅ አድነኝ” ሲል መልእክተኞች ላከበት። 8አካዝም በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስና በቤተ መንግሥቱ ግምጃ ቤቶች የሚገኘውን ብርና ወርቅ አውጥቶ ለአሦር ንጉሥ ገጸ በረከት ላከለት። 9የአሦር ንጉሥም፣ የአካዝን ልመና በመቀበል፤ ደማስቆን አጥቅቶ ያዛት፤ ሕዝቧን ማርኮ ወደ ቂር አፈለሳቸው፤ ረአሶንንም ገደለው።

10ከዚያም ንጉሥ አካዝ የአሦርን ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶርን ለመገናኘት ወደ ደማስቆ ሄደ። በደማስቆም ያለውን መሠዊያ አይቶ፣ ንድፉን ከዝርዝር ጥናቱ ጋር ለካህኑ ለኦርያ ላከለት። 11ካህኑ ኦርያም ንጉሥ አካዝ ከደማስቆ በላከለት ዝርዝር ጥናት መሠረት መሠዊያ ሠራ፤ ንጉሡ አካዝ ከመመለሱም በፊት አጠናቀቀው። 12ንጉሡ ከደማስቆ ተመልሶ በመጣ ጊዜ፣ መሠዊያውን አየ፤ ቀርቦም በመሠዊያው ላይ ወጣ፤ 13ከዚያም የሚቃጠል መሥዋዕቱንና የእህል ቍርባኑን በመሠዊያው ላይ አቀረበ፤ የመጠጥ ቍርባኑን አፈሰሰ፤ የኅብረት መሥዋዕቱንም16፥13 በትውፊት፣ የሰላም መሥዋዕት ደም በመሠዊያው ላይ ረጨ። 14በአዲሱ መሠዊያና በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መካከል፣ በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ የነበረውን የናስ መሠዊያ፣ ከቦታው አስነሥቶ ከአዲሱ መሠዊያ በስተ ሰሜን በኩል አኖረው።

15ከዚያም ንጉሥ አካዝ፣ ካህኑን ኦርያን እንዲህ ሲል አዘዘው፤ “በዚህ በትልቁ አዲስ መሠዊያ ላይ የጧቱን የሚቃጠል መሥዋዕትና የማታውን የእህል ቍርባን፣ የንጉሡን የሚቃጠል መሥዋዕትና የእህሉን ቍርባን እንዲሁም የመላውን የአገሪቱን ሕዝብ የሚቃጠል መሥዋዕት፣ የእህልና የመጠጥ ቍርባናቸውን አቅርብ፤ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ደምና የሌላውን መሥዋዕት ደም ሁሉ በመሠዊያው ላይ እርጨው፤ የናሱ መሠዊያ ግን እኔ መመሪያ ለመጠየቅ የምጠቀምበት ይሆናል።” 16ካህኑ ኦርያም ንጉሡ አካዝ እንዳዘዘው ሁሉ እንዲሁ አደረገ።

17ንጉሡ አካዝም የጐንና የጐን ሳንቃዎቹን ነቅሎ ወሰደ፤ በተንቀሳቃሹ መቆሚያ ላይ ያሉትን የመታጠቢያ ሳሕኖች አስወገደ። የውሃ ማጠራቀሚያውን ክብ ገንዳ ከታች ተሸክመው ከያዙት ከዐሥራ ሁለቱ የናስ ቅርጽ ኮርማዎች ላይ አውርዶ በጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ አስቀመጠው። 18የአሦርንም ንጉሥ ለማስደሰት ሲል፣ በዕለተ ሰንበት ንጉሣዊ ዙፋን16፥18 የሰብዓ ሊቃናት መሥዋዕት ትርጕም፣ የዙፋኑ ሰሌዳ ይላል። እንዲዘረጋበት በቤተ መቅደሱ ውስጥ የተሠራውን ከፍ ያለ ስፍራና ነገሥታቱ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሚገቡበትን በውጭ ያለውን መግቢያ አነሣ።

19በአካዝ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ሥራ፣ የፈጸመውም ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 20አካዝም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ከእነርሱ ጋር በዳዊት ከተማ ተቀበረ። ልጁ ሕዝቅያስም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

Thai New Contemporary Bible

2พงศ์กษัตริย์ 16:1-20

กษัตริย์อาหัสแห่งยูดาห์

(2พศด.28:1-27)

1อาหัสโอรสกษัตริย์โยธามแห่งยูดาห์ขึ้นครองราชย์ตรงกับปีที่สิบเจ็ดของรัชกาลกษัตริย์เปคาห์บุตรเรมาลิยาห์ 2ขณะนั้นทรงมีพระชนมายุยี่สิบพรรษา และทรงครองราชย์อยู่ในกรุงเยรูซาเล็มสิบหกปี อาหัสไม่ได้ทรงทำสิ่งที่ถูกต้องในสายพระเนตรของพระยาห์เวห์พระเจ้าของพระองค์เหมือนที่ดาวิดผู้เป็นบรรพบุรุษเคยทำ 3แต่ทรงทำตามอย่างกษัตริย์ทั้งหลายของอิสราเอล ถึงกับนำโอรสของพระองค์มาเผาบูชายัญ16:3 หรือให้ลุยไฟเป็นเครื่องบูชาตามแบบอย่างอันน่าชิงชังของชนชาติต่างๆ ที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงขับไล่ออกไปให้พ้นหน้าชาวอิสราเอล 4อาหัสถวายเครื่องบูชาและเผาเครื่องหอมตามสถานบูชาบนที่สูงทั้งหลาย บนเนินเขาต่างๆ และใต้ต้นไม้ใหญ่ทุกต้น

5ต่อมากษัตริย์เรซีนแห่งอารัมและกษัตริย์เปคาห์บุตรเรมาลิยาห์แห่งอิสราเอลกรีธาทัพมารบกับอาหัสและล้อมกรุงเยรูซาเล็ม แต่พิชิตไม่ได้ 6ครั้งนั้นกษัตริย์เรซีนแห่งอารัมทรงยึดเอลัทคืนให้อารัม โดยขับไล่ชาวยูดาห์ออกไป แล้วชาวเอโดมจึงเข้าไปอาศัยอยู่ที่เอลัทตราบจนทุกวันนี้

7อาหัสทรงส่งทูตไปแจ้งกษัตริย์ทิกลัทปิเลเสอร์แห่งอัสซีเรียว่า “ข้าพเจ้าเป็นผู้รับใช้ของท่านและผู้สวามิภักดิ์ต่อท่าน ขอโปรดมาช่วยรบกับทัพอารัมและอิสราเอลซึ่งยกมาโจมตีข้าพเจ้าด้วยเถิด” 8อาหัสได้นำทองคำและเงินที่มีในพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าและคลังหลวงส่งไปบรรณาการแด่กษัตริย์อัสซีเรีย 9กษัตริย์อัสซีเรียจึงโจมตีและยึดเมืองดามัสกัส ประหารเรซีน แล้วกวาดต้อนชาวเมืองไปเป็นเชลยที่เมืองคีร์

10กษัตริย์อาหัสเสด็จไปที่เมืองดามัสกัสเพื่อเข้าเฝ้ากษัตริย์ทิกลัทปิเลเสอร์แห่งอัสซีเรีย พระองค์ทรงเห็นแท่นบูชาที่เมืองดามัสกัส จึงส่งแบบร่างและรายละเอียดในการสร้างแท่นบูชามาให้ปุโรหิตอุรียาห์ 11ดังนั้นปุโรหิตอุรียาห์จึงสร้างแท่นบูชาขึ้นมาอีกแท่นหนึ่งตามแบบที่กษัตริย์อาหัสส่งมาจากเมืองดามัสกัสทุกประการ และสร้างเสร็จก่อนที่กษัตริย์อาหัสจะเสด็จกลับมา 12เมื่อกษัตริย์เสด็จกลับมาจากเมืองดามัสกัสและเห็นแท่น ก็ถวายเครื่องบูชาบนแท่นนั้น 13ทรงถวายเครื่องเผาบูชา ธัญบูชา เครื่องดื่มบูชา และประพรมเลือดจากเครื่องสันติบูชาบนแท่นนั้น 14ส่วนแท่นบูชาทองสัมฤทธิ์ซึ่งอยู่ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าแท่นเดิมนั้น พระองค์ทรงย้ายจากด้านหน้าของพระวิหาร คือระหว่างแท่นบูชาใหม่กับพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า ไปตั้งไว้ด้านทิศเหนือของแท่นบูชาใหม่

15กษัตริย์อาหัสทรงบัญชาปุโรหิตอุรียาห์ว่า “จงใช้แท่นบูชาใหม่นี้สำหรับถวายเครื่องเผาบูชายามเช้า ธัญบูชายามเย็น เครื่องเผาบูชากับธัญบูชาของกษัตริย์ และเครื่องเผาบูชากับธัญบูชาและเครื่องดื่มบูชาของประชากร และประพรมเลือดจากเครื่องเผาบูชาและเครื่องบูชาต่างๆ ที่แท่นใหม่นี้ด้วย ส่วนแท่นทองสัมฤทธิ์นั้น เราจะใช้สำหรับขอคำแนะนำ” 16ปุโรหิตอุรียาห์ก็ทำตามพระบัญชาของกษัตริย์อาหัส

17กษัตริย์อาหัสทรงรื้อแผงด้านข้างของแท่นเคลื่อนที่ทองสัมฤทธิ์ และย้ายขันบรรจุน้ำที่วางบนแท่นออกไป พระองค์ทรงย้ายขันสาครจากหลังของวัวทองสัมฤทธิ์ไปตั้งไว้บนฐานหิน 18และเพื่อเอาใจกษัตริย์อัสซีเรีย อาหัสทรงย้ายศาลาสะบาโตไปจากพระวิหาร แล้วปิดทางพระราชดำเนินส่วนพระองค์ด้านนอกที่มายังพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า

19เหตุการณ์อื่นๆ ในรัชกาลของอาหัสมีบันทึกอยู่ในจดหมายเหตุกษัตริย์แห่งยูดาห์ไม่ใช่หรือ? 20อาหัสทรงล่วงลับไปอยู่กับบรรพบุรุษและถูกฝังไว้ร่วมกันในเมืองดาวิด แล้วเฮเซคียาห์โอรสของพระองค์ขึ้นครองราชย์แทน