2 ሳሙኤል 23 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 23:1-39

የዳዊት የመጨረሻ ቃል

1የዳዊት የመጨረሻ ቃሉ ይህ ነው፤

“በያዕቆብ አምላክ የተቀባው፣

ልዑል ከፍ ከፍ ያደረገው ሰው፣

የእስራኤል ተወዳጁ ዘማሪ፣

የእሴይ ልጅ የዳዊት የትንቢት ቃል ይህ ነው፤

2የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ተናገረ፤

ቃሉ በአንደበቴ ላይ ነበረ።

3የእስራኤል አምላክ ተናገረ፤

የእስራኤልም ዐለት እንዲህ አለኝ፤

‘ሰዎችን በጽድቅ የሚገዛ፣

በፈሪሀ እግዚአብሔርም የሚያስተዳድር፣

4እርሱ፣ ደመና በሌለበት፣ በማለዳ ፀሓይ በምትወጣበት ጊዜ፣

እንዳለው ብርሃን ነው፤

በምድር ላይ ሣርን እንደሚያበቅለው፣

ከዝናብም በኋላ እንዳለው የብርሃን ጸዳል ነው።’

5“የእኔስ ቤት በእግዚአብሔር ዘንድ ትክክል አይደለምን?

ሁሉንም ነገር አዘጋጅቶና ጠብቆ፣

ከእኔ ጋር ዘላለማዊ ኪዳን ያደረገ አይደለምን?

ድነቴን ከፍጻሜ የሚያደርሰው፣

መሻቴን ሁሉ የሚሰጠኝ እርሱ አይደለምን?

6ነገር ግን ክፉ ሰዎች ሁሉ፣

በእጅ እንደማይሰበሰብ እንደ እሾኽ ይጣላሉ።

7እሾኽ የሚነካ ሁሉ፣

የብረት መሣሪያ ወይም የጦር ዘንግ ይይዛል፤

ባሉበትም ቦታ ፈጽመው በእሳት ይቃጠላሉ።”

የኀያላኑ የዳዊት ሰዎች ጀብዱ

23፥8-39 ተጓ ምብ – 1ዜና 11፥10-41

8የዳዊት ኀያላን ሰዎች ስም የሚከተለው ነው፤

የታሕክሞን23፥8 የታሕክሞን ሰው ማለት ሐክሞናዊ ማለት ሊሆን ይችላል። (1ዜና 11፥11 ይመ)። ሰው ዮሴብ በሴትቤት23፥8 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ግን፣ ኢያሱስቴ ይላሉ፣ ይኸውም፣ ያሾብዓም ነው (1ዜና 11፥11 ይመ)። የሦስቱ አለቆች አለቃ ሲሆን፣ እርሱም ጦሩን ሰብቆ በአንድ ውጊያ ላይ ስምንት መቶ ሰው የገደለ ነው።23፥8 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ (1ዜና 11፥11 ይመ)፤ ዕብራይስጡና አብዛኞቹ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ግን ስምንት መቶ ሰዎችን የገደለው አዜናዊው አዲኑ ነበር ይላሉ።

9ከእርሱ ቀጥሎ የአሆሃዊው የዱዲ ልጅ ኤልዔዘር ነበረ፤ እርሱም ለጦርነት አንድ ላይ ተሰብስበው23፥9 1ዜና 11፥13 ይመ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ በዚያ ተሰበሰቡ ይላል የነበሩትን ፍልስጥኤማውያንን በተገዳደሩ ጊዜ፣ ከዳዊት ጋር ከነበሩት ከሦስቱ ኀያላን ሰዎች አንዱ ነበር። ከዚያም የእስራኤል ሰዎች ሸሹ። 10እርሱ ግን የቆመበትን ስፍራ አልለቀቀም፤ እጁ እስኪዝልና ከሰይፉ ጋር እስኪጣበቅ ድረስ ፍልስጥኤማውያንን ወጋ፤ በዚያችም ዕለት እግዚአብሔር ታላቅ ድልን ሰጠ። የሸሸውም ሰራዊት ወደ ኤልዔዘር የተመለሰው የተገደሉትን ሰዎች ለመግፈፍ ብቻ ነበር።

11ከእርሱም ቀጥሎ የአሮዳዊው የአጌ ልጅ ሣማ ነበር፤ ፍልስጥኤማውያንም ሌሒ በተባለ ስፍራ ምስር በሞላበት አንድ ዕርሻ ላይ በአንድነት ተሰብስበው ሳሉ፣ የእስራኤል ሰራዊት ከፍልስጥኤማውያን ፊት ሸሹ፤ 12ሣማ ግን የቆመበትን ስፍራ አልለቀቀም፤ ጦርነቱንም ተቋቁሞ ፍልስጥኤማውያንን ገደለ፤ በዚያችም ዕለት እግዚአብሔር ታላቅ ድል ሰጠ።

13በመከር ወራት፣ የፍልስጥኤም ሰራዊት በራፋይም ሸለቆ ሰፍሮ ሳለ፣ ከሠላሳዎቹ አለቆች ሦስቱ ዳዊት ወዳለበት ወደ ዓዶላም ዋሻ መጡ። 14በዚያም ጊዜ ዳዊት በምሽግ ውስጥ ነበረ፤ የፍልስጥኤማውያንም ሰራዊት በቤተ ልሔም ነበረ፤ 15ዳዊትም በናፍቆት፣ “በቤተ ልሔም በር አጠገብ ካለችው ጕድጓድ ውሃ ማን ባመጣልኝ!” አለ። 16ስለዚህ ሦስቱ ኀያላን በፍልስጥኤማውያን ሰራዊት መካከል ሰንጥቀው በማለፍ፣ በቤተ ልሔም በር አጠገብ ካለችው ጕድጓድ ውሃ ቀድተው ለዳዊት አመጡለት። እርሱ ግን አልጠጣውም፤ ይልቁን በእግዚአብሔር ፊት መሥዋዕት አድርጎ አፈሰሰው፤ 17“እርሱም፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንዲህ ያለውን ነገር ላደርግ? ይህስ ከእኔ ይራቅ! ይህ በነፍሳቸው ቈርጠው የሄዱ ሰዎች ደም አይደለምን?” አለ፤ ዳዊትም ሊጠጣው አልፈለገም። እንግዲህ ሦስቱ ኀያላን ሰዎች ያደረጉት ጀብዱ እንዲህ ነበር።

18የጽሩያ ልጅ የኢዮአብ ወንድም አቢሳ የሦስቱ23፥18 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች (እንዲሁም 1ዜና 11፥20 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ሁለት የዕብራይስጥ ቅጆችና የሱርስቱ ትርጕም፣ ሠላሳ ይላሉ። ኀያላን አለቃ ነበረ። በሦስት መቶ ሰዎች ላይ ጦሩን ሰብቆ የገደላቸውና እንደ ሦስቱ ኀያላን ሁሉ እርሱም ዝናን ያተረፈ ሰው ነበረ። 19አቢሳ ከሦስቱ ይልቅ እጅግ የከበረ አልነበረምን? ከእነርሱ እንደ አንዱ ባይሆንም አለቃቸው ነበረ።

20የቀብጽኤል አገር ሰው የሆነው የዮዳሄ ልጅ በናያስ ታላቅ ጀብዱ የሠራ ሌላው ጐበዝ ተዋጊ ነበረ፤ እርሱም ሁለት በጣም የታወቁ የሞዓብ ሰዎችን ገደለ፤ እንዲሁም በረዶ በጣለበት ዕለት በጕድጓድ ውስጥ ገብቶ አንበሳ ገድሏል፤ 21ደግሞም አንድ ግዙፍ ግብፃዊ ገድሏል፤ ግብፃዊው በእጁ ጦር የያዘ ቢሆንም፣ በናያስ ግን ሊገጥመው በትር ይዞ ወደ እርሱ ሄደ፤ ከግብፃዊውም እጅ ጦሩን በመንጠቅ በገዛ ጦሩ ገደለው።

22የዮዳሄ ልጅ የበናያስ ጀግንነት እንደዚህ ያለ ነበረ፤ እርሱም እንደ ሦስቱ ኀያላን ሁሉ ዝናን ያተረፈ ሲሆን፣ 23ከሠላሳዎቹ ሁሉ በላይ የከበረ ሰው ነበረ፤ ነገር ግን ከሦስቱ እንደ አንዱ አልነበረም። ዳዊትም የክብር ዘበኞቹ አለቃ አድርጎ ሾመው።

24ከሠላሳዎቹ መካከል የሚከተሉት ይገኙባቸዋል፤

የኢዮአብ ወንድም አሣሄል፣

የቤተ ልሔሙ ሰው የዱዲ ልጅ ኤልያናን፣

25አሮዳዊው ሣማ፣

አሮዳዊው ኤሊቃ፣

26ፈሊጣዊው ሴሌስ፣

የቴቁሐዊው የዒስካ ልጅ ዒራስ፣

27ዓናቶታዊው አቢዔዜር፤

ኩሳታዊው ምቡናይ23፥27 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 11፥29 ይመ) ግን፣ ሲባካይ ይላሉ።

28አሆሃዊው ጸልሞን፣

ነጦፋዊው ማህራይ፣

29የነጦፋዊው የበዓና ልጅ ሔሌብ23፥29 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆችና ቩልጌት (እንዲሁም 1ዜና 11፥30 ይመ) ግን፣ ሔሌድ ይላሉ።

ከብንያም ወገን የጊብዓ ሰው የሆነው የሪባይ ልጅ ኢታይ፣

30ጲርዓቶናዊው በናያስ፣

የገዓስ ሸለቆ ሰው ሂዳይ23፥30 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 11፥32 ይመ) ግን፣ ሁራይ ይላሉ።

31ዐረባዊው አቢዓልቦን፣

በርሑማዊው ዓዝሞት፣

32ሸዓልቦናዊው ኤሊያሕባ፣

የአሳን ልጆች፤ ዮናታን የተባለው፣

33የአሮዳዊው የሣማ ልጅ23፥33 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 11፥34 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን ልጅ የሚለውን አይጨምርም።

የአሮዳዊው የሻራር23፥33 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም 1ዜና 11፥35 ይመ) ግን፣ ሳካር ይላሉ። ልጅ አሒአም፤

34የማዕካታዊው የአሐሰባይ ልጅ ኤሌፋላት፣

የጊሎናዊው የአኪጦፌል ልጅ ኤሊአም፣

35ቀርሜሎሳዊው ሐጽሮ፤

አርባዊው ፈዓራይ፣

36የሱባ ሰው የሆነው የናታን ልጅ ይግዓል፣

37አሞናዊው ጻሌቅ፣

የጽሩያ ልጅ የኢዮአብ ጦር መሣሪያ ያዥ የነበረው ብኤሮታዊው ነሃራይ፣

38ይትራዊው ዒራስ፣

ይትራዊው ጋሬብ፣

39እንዲሁም ኬጢያዊው ኦርዮ።

በጠቅላላው ሠላሳ ሰባት ነበሩ።

O Livro

2 Samuel 23:1-39

As últimas palavras de David

1Estas foram as últimas palavras de David:

“Diz assim David, o filho de Jessé,

o homem a quem Deus deu tanto sucesso,

o ungido do Deus de Jacob,

o suave salmista de Israel.

2O Espírito do Senhor falou por mim,

a sua palavra estava na minha boca.

3Disse-me assim a rocha de Israel:

‘Aquele que governa com toda a justiça,

que administra no temor de Deus,

4é como a luz da manhã,

como uma esplêndida alvorada,

quando a tenra erva brota do solo,

sob o calor do Sol, depois da chuva.’

5Foi igualmente a minha família que ele escolheu!

Sim, Deus estabeleceu uma aliança eterna comigo;

está selada com o seu acordo eterno.

Zelará constantemente pela minha segurança

e pelo meu sucesso.

6Os ímpios são como espinhos

que se lançam para longe;

rasgam a mão de quem lhes pega.

7Tem de se estar protegido para os apanhar,

e para serem lançados no fogo.”

Os grandes chefes militares de David

(1 Cr 11.10-41)

8São os seguintes os nomes dos três homens mais valentes que David teve, os mais heróicos soldados do seu exército: O primeiro foi Josebe-Bassebete, de Taquemoni, também conhecido por Adino, o eznita; certa vez matou 800 homens numa só batalha.

9Depois é Eleazar, o filho de Dodo e neto de Aoí. Foi um dos três homens que, com David, enfrentaram os filisteus daquela vez que o exército de Israel fugiu. 10Matou filisteus, até que a sua mão, de cansada, já lhe doía ao segurar a espada; o Senhor deu-lhe uma grande vitória. O resto do exército só voltou na altura de recolher o despojo.

11-12A seguir, vem Samá, filho de Agé, de Harar. Uma vez, no decorrer dum ataque filisteu, quando todos os seus homens o tinham deixado só e fugido, ficou sozinho no meio dum campo de lentilhas e conseguiu pôr em debandada os filisteus. Também a este o Senhor deu uma grande vitória.

13Um dia, quando David vivia na caverna de Adulão e os invasores filisteus estavam no vale de Refaim, três dos trinta oficiais comandantes do exército israelita desceram no tempo da sega para o visitar. 14No momento do acontecimento David encontrava-se numa fortaleza. Uns guerreiros filisteus tinham ocupado Belém. 15A certa altura, David expressou o seguinte desejo: “Quem me dera poder beber da água daquele poço de Belém que está junto à porta!” 16Então esses três homens romperam através desse posto avançado dos filisteus, tiraram água do poço e trouxeram-na a David! Contudo, David recusou; em vez de a beber, derramou-a como oferta perante o Senhor. 17E disse: “Nunca faria tal coisa, Senhor! Nunca beberia uma água que afinal representa o sangue destes homens que arriscaram as suas vidas para a ir buscar!”

18Também Abisai, irmão de Joabe, filho de Zeruía, foi comandante dos trinta. Certa vez, só com a sua lança, matou 300 soldados inimigos. 19Foi por tais feitos que ele ganhou uma reputação semelhante à daqueles três homens, ainda que não fosse igual a eles. Entre o corpo dos trinta comandantes, ele era o chefe.

20Havia também Benaia, filho de Jeoiada, um valente soldado de Cabzeel. Benaia matou os dois filhos de Ariel de Moabe. Noutra altura, entrou numa gruta e a despeito do chão estar muito escorregadio, por causa da neve gelada, pegou num leão que ali se tinha abrigado e matou-o. 21Noutra ocasião ainda, tendo na mão unicamente uma vara, matou um soldado egípcio armado com uma lança; conseguiu arrancar-lha e com ela matou o egípcio. 22Estes foram alguns dos feitos que deram a Benaia, filho de Jeoiada, quase tanta fama como a dos três primeiros. 23Era muito famoso entre os trinta, mas não pode rivalizar com o grupo dos três. David fê-lo capitão da sua guarda pessoal.

24Asael, irmão de Joabe, era também um dos trinta comandantes. Os outros eram:

El-Hanã, filho de Dodo, de Belém;

25Samá de Harode;

Elica também de Harode;

26Helez de Palti;

Ira, filho de Iques, de Tecoa;

27Abiezer de Anatote;

Mebunai de Husate;

28Zalmom o aoíta;

Maarai de Netofá;

29Helebe, filho de Baaná, de Netofá;

Itai, filho de Ribai, de Gibeá, da tribo de Benjamim;

30Benaia de Piraton;

Hidai do ribeiro de Gaás;

31Abi-Albom de Arbate;

Azmavete de Baurim;

32Eliaba de Saalbom;

Os filhos de Jasen;

Jónatas, filho de Sage, de Harar;

33Samá de Harar;

Aião, filho de Sarar, de Harar;

34Elifelete, filho se Aasbai, de Maacá;

Eliam, filho de Aitofel, de Gilo;

35Hezro do Carmelo;

Paarai de Arba;

36Igal, filho de Natã, de Zobá;

Bani de Gad;

37Zeleque de Amon;

Naarai de Beerote, o que levava as armas de Joabe, o filho de Zeruía;

38Ira de Itra;

Garebe de Itra;

39Urias, o hitita.

Trinta e sete ao todo.