1 ነገሥት 4 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 4:1-34

የሰሎሞን ሹማምት

1ንጉሥ ሰሎሞን በእስራኤል ሁሉ ላይ ነገሠ፤

2ዋና ዋናዎቹ ሹማምቱም እነዚህ ነበሩ፤

የሳዶቅ ልጅ ዓዛርያስ፣ ካህን፤

3የሺሻ ልጆች ኤሊሖሬፍና አኪያ፣ ጸሓፊዎች፤

የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ፣ ታሪክ ጸሓፊ፤

4የዮዳሄ ልጅ በናያስ፣ የሰራዊቱ ዋና አዛዥ፤

ሳዶቅና አብያታር፣ ካህናት፤

5የናታን ልጅ ዓዛርያስ፣ የአውራጃ ገዦች የበላይ ኀላፊ፤

የናታን ልጅ ዛቡድ፣ ካህንና የንጉሡ የቅርብ አማካሪ፤

6አሒሳር፣ የቤተ መንግሥቱ አዛዥ፤

የዓብዳ ልጅ አዶኒራም የግዳጅ ሥራ ተቈጣጣሪ።

7እንዲሁም ሰሎሞን ለንጉሡና ለንጉሡ ቤት የሚሆነውን ቀለብ ከመላው እስራኤል የሚሰበስቡ ዐሥራ ሁለት የአውራጃ ገዦች ነበሩት፤ እነዚህም እያንዳንዳቸው በዓመት ውስጥ የወር ቀለብ የሚያቀርቡ ነበሩ።

8ስማቸውም እንደሚከተለው ነው፤

ቤንሑር፣ በኰረብታማው በኤፍሬም ምድር፤

9ቤንጼቄር፣ በማቃጽ፣ በሻዓልቢም፣ በቤትሳሜስ፣ በኤሎንቤትሐናን፤

10ቤንሔሴድ፣ በአሩቦት ውስጥ የሚገኙት ሰኰትና የኦፌር አገር በሙሉ የእርሱ ነበር፤

11ቤን አሚናዳብ፤ በናፎት ዶር፣ እርሱም የሰሎሞንን ልጅ ጣፈትን አግብቶ የነበረ ነው፤4፥11 ወይም በናፎት ቁመት ተብሎ ሊተረጐም ይችላል።

12የአሒሉድ ልጅ በዓና፣ በታዕናክና በመጊዶ እንዲሁም ከጻርታን ቀጥሎ ቍልቍል እስከ ኢይዝራኤል ባለው በቤትሳን ሁሉ፣ ከዚያም ዮቅምዓምን ተሻግሮ እስከ አቤልምሖላና ድረስ፣

13ቤንጌበር፣ በገለዓድ ራሞት ከተማ እዚያው ገለዓድ ውስጥ የምናሴ ልጅ የኢያዕር መንደሮች፣ በባሳንም የአርጎብ አውራጃ እንዲሁም በሮቻቸው የናስ መወርወሪያ በሆኑ ስድሳ ባለ ቅጥር ታላላቅ ከተሞች፤

14የዒዶ ልጅ አሒናዳብ፤ በማሃናይም፣

15አኪማአስ በንፍታሌም፣ እርሱም የሰሎሞንን ልጅ ባስማትን አግብቶ የነበረ ነው፤

16የኩሲ ልጅ በዓና፤ በአሴርና በበዓሎት፣

17የፋሩዋ ልጅ ኢዮሣፍጥ በይሳኮር፣

18የኤላ ልጅ ሳሚ በብንያም፣

19የኡሪ ልጅ ጌበር፤ በአሞራውያን ንጉሥ በሴዎን ምድር፣ በባሳን ንጉሥ በዐግ አገር፣ እርሱም የአውራጃው ብቸኛ ገዥ ነበር።

ለሰሎሞን በየቀኑ የሚገባለት ቀለብ

20የይሁዳና የእስራኤል ሕዝቦች ብዛታቸው እንደ ባሕር ዳር አሸዋ ሆነ፤ ይበሉ፣ ይጠጡና ይደሰቱም ነበር። 21ሰሎሞንም ከወንዙ4፥21 በዚህና በ24 ላይ የተጠቀሰው የኤፍራጥስ ወንዝ ነው። አንሥቶ እስከ ፍልስጥኤማውያን ምድር፣ ከዚያም እስከ ግብፅ ዳርቻ ያሉትን መንግሥታት ሁሉ ገዛ፤ እነዚህም አገሮች ግብር አመጡለት፤ በሕይወት ዘመኑም ሁሉ ተገዙለት።

22ለሰሎሞን በየቀኑ የሚገባለትም ቀለብ ይህ ነበር፤ ሠላሳ ኮር4፥22 5500 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ማለፊያ ዱቄት፣ ስድሳ ኮር4፥22 11000 ኪሎ ግራም ያህል ነው። መናኛ ዱቄት፣ 23ዐሥር ቅልብ ሰንጋዎች፣ ሃያ ግጦሽ መሬት ላይ የሚውሉ በሬዎች፣ መቶ በግና ፍየል እንዲሁም ዋሊያ፣ ሚዳቋ፣ የበረሓ ፍየልና ምርጥ አዕዋፍ። 24ከወንዙ በስተ ምዕራብ፣ ከቲፍሳ እስከ ጋዛ ያሉትን መንግሥታት ስለ ገዛ፣ በሁሉም አቅጣጫ ሰላም ሆኖለት ነበር። 25በሰሎሞን ዘመን ሁሉ ከዳን አንሥቶ እስከ ቤርሳቤህ ያለው ይሁዳና እስራኤል፣ እያንዳንዱ ሰው ከወይኑና ከበለሱ ጥላ ሥር በሰላም ለመኖር በቃ።

26ሰሎሞን ሠረገላ የሚጐትቱ ፈረሶች የሚያድሩበት አራት ሺሕ ጋጣና ዐሥራ ሁለት ሺሕ ፈረሶች4፥26 ዕብራይስጡና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች አርባ ይላሉ። ነበሩት4፥26 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይችላል።

27የየአውራጃው ሹማምትም በየወር ተራቸው ንጉሡን ሰሎሞንንና ወደ ንጉሡ ማእድ የሚቀርቡትን ሁሉ ምንም ሳያጓድሉ ይቀልቡ ነበር፤ 28እንዲሁም ለሠረገላ ፈረሶችና ለፈጣን ፈረሶች የተመደበውን ገብስና ጭድ ከተፈለገው ቦታ ድረስ ያመጡ ነበር።

የሰሎሞን ጥበብ

29አምላክ ለሰሎሞን ጥበብንና እጅግ ታላቅ ማስተዋልን እንዲሁም በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ የልብ ስፋትን ሰጠው። 30የሰሎሞን ጥበብ ከምሥራቅ ሰዎች ሁሉ ጥበብ በጣም የላቀ ከግብፅም ጥበብ ሁሉ የበለጠ ነበር፤ 31እርሱም ከማንም ሰው ይልቅ ጥበበኛ ነበር፣ ከኢይዝራኤላዊው ከኤታን፣ ከማሖል ልጆች ከሄማንና ከከልቀድ ደግሞም ከደራል ይልቅ ጥበበኛ ነበር፤ ዝናውም በዙሪያው ባሉት አሕዛብ ሁሉ ተሰማ። 32እርሱም ሦስት ሺሕ ምሳሌዎችን ተናገረ፤ የመሓልዩም ቍጥር ሺሕ አምስት ነበር። 33ከሊባኖስ ዝግባ አንሥቶ በቅጥር ግንብ ላይ እስከሚበቅለው ሂሶጵ ስለ ዕፀዋት ተናግሯል፤ እንዲሁም ስለ እንስሳት፣ ስለ ወፎች፣ በሆዳቸው ስለሚሳቡ እንስሳትና ስለ ዓሦችም ተናግሯል፤ 34ጥበቡን ከሰሙት ከዓለም ነገሥታት ሁሉ የተላኩ፣ የየአገሩ ሰዎች ሁሉ የሰሎሞንን ጥበብ ለማድመጥ መጡ።

Persian Contemporary Bible

اول پادشاهان 4:1‏-34

مقامات دربار سليمان

1‏-6سليمان پادشاه بر تمام اسرائيل حكومت می‌كرد و مقامات دربار او عبارت بودند از:

عزريا (پسر صادوق)، رئيس كاهنان؛

اليحورف و اخيا (پسران شيشه)، کاتب؛

یهوشافاط (پسر اخيلود)، وقايع‌نگار؛

بنايا (پسر يهوياداع)، فرماندهٔ سپاه؛

صادوق و ابياتار، كاهن؛

عزريا (پسر ناتان)، سرپرست حاكمان؛

زابود (پسر ناتان)، كاهن و مشاور پادشاه؛

اخيشار، سرپرست امور دربار؛

ادونيرام (پسر عبدا) سرپرست كارهای اجباری.

7سليمان در تمام اسرائيل دوازده حاكم گماشته بود و آنها وظيفه داشتند خوراک دربار را تهيه كنند. هر يک از ايشان، يک ماه در سال مسئول تداركات دربار بودند.

8‏-19اين است اسامی دوازده حاكم و حوزه‌های فعاليت آنها:

بن هور، در كوهستان افرايم؛

بن دقر، در ماقص، شعلبيم، بيت‌شمس، ايلون و بيت حانان؛

بن حسد، در اربوت، سوكوه و تمامی قلمرو حافر؛

بن ابيناداب، (كه با تافَت دختر سليمان ازدواج كرده بود) در تمام منطقهٔ دُر؛

بعنا (پسر اخيلود)، در تعنک، مجدو، تمام سرزمين نزديک بيت‌شان و صرتان، جنوب شهر يزرعيل، و تا شهر آبل مهوله و شهر يقمعام.

بن جابر، در راموت جلعاد كه شامل دهكده‌های ياعير (پسر منسی) در جلعاد و ناحيه ارجوب در باشان می‌شد با شصت شهر حصاردار ديگر كه دروازه‌هايشان پشت‌بندهای مفرغی داشت؛

اخيناداب (پسر عدو)، در محنايم؛

اخيمعص (كه با باسمت دختر ديگر سليمان ازدواج كرده بود)، در نفتالی؛

بعنا (پسر حوشای)، در اشير و بعلوت؛

يهوشافاط (پسر فاروح)، در سرزمين يساكار؛

شمعی (پسر ايلا)، در سرزمين بنيامين؛

جابر (پسر اوری)، در جلعاد كه شامل سرزمينهای سيحون، پادشاه اموری‌ها و عوج، پادشاه باشان می‌شد.

اين دوازده حاكم زير نظر حاكم كل قرار داشتند.

حكمت و عظمت سليمان

20در آن زمان اسرائيل و يهودا قوم بزرگ و مرفه و كاميابی بودند. 21سليمان بر تمام سرزمينهای واقع در بين رود فرات و فلسطين كه تا سرحد مصر نيز می‌رسيدند سلطنت می‌كرد. اقوام اين سرزمينها به او باج و خراج می‌دادند و در تمام مدت عمرش تابع او بودند.

22آذوقهٔ روزانهٔ دربار عبارت بود از: حدود پنج تن آرد و ده تن بلغور، 23ده گاو از طويله، بيست گاو از چراگاه، صد گوسفند و نيز غزال، آهو، گوزن و انواع مرغان.

24قلمرو سلطنت سليمان از تفصح تا غزه می‌رسيد و تمام ممالک غرب رود فرات را در بر می‌گرفت. تمام پادشاهان غرب رود فرات تابع او بودند و او با سرزمينهای همسايه در صلح بود.

25مردم يهودا و اسرائيل در طول سلطنت سليمان در كمال آرامش بودند و هر خانواده زير درختان مو و انجير خود آسوده می‌نشستند.

26سليمان دوازده هزار اسب و چهار هزار اصطبل برای اسبان عرابه‌های خود داشت.

27حاكمان، هر يک در ماه تعيين شده، خوراک سليمان و مهمانان او را بدون كم و كسر تهيه می‌كردند. 28در ضمن هر يک به سهم خود برای اسبان عرابه و ساير اسبان كاه و جو فراهم می‌ساختند.

29خدا به سليمان فهم و حكمت بی‌نظيری بخشيد و بصيرت او بی‌حد و حصر بود. 30حكمت سليمان از حكمت دانشمندان مشرق زمين و علمای مصر هم زيادتر بود. 31او حتی از حكمای معروفی چون ايتان ازراحی و پسران ماحول يعنی حيمان و كلكول و دَردَع حكيمتر بود. سليمان در ميان تمام ممالک دنيای زمان خود معروف شد. 32سه هزار مثل گفت و هزار و پنج سرود نوشت. 33سليمان دربارهٔ حيوانات و پرندگان و خزندگان و ماهيان اطلاع كافی داشت، او همچنين تمام گياهان را از درختان سرو گرفته تا بوته‌های كوچک زوفا كه در شكاف ديوارها می‌رويند، می‌شناخت و دربارهٔ آنها سخن می‌گفت. 34پادشاهان سراسر جهان كه آوازهٔ حكمت او را شنيده بودند نمايندگانی به دربار او می‌فرستادند تا از حكمتش برخوردار شوند.