1 ቆሮንቶስ 8 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 8:1-13

ለጣዖት የተሠዋ ሥጋ

1ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋ ደግሞ ይህን እላለሁ፤ ሁላችንም ዕውቀት እንዳለን እናውቃለን8፥1 ወይም እናንተ እንደምትሉት “ሁላችንም ዕውቀት አለን”። ዕውቀት ያስታብያል፤ ፍቅር ግን ያንጻል። 2ዐውቃለሁ የሚል ሰው፣ ማወቅ የሚገባውን ያህል ገና አላወቀም። 3እግዚአብሔርን የሚወድድ ሰው ግን በእግዚአብሔር ዘንድ የታወቀ ነው።

4እንግዲህ፣ ለጣዖት የተሠዋ ሥጋ ስለ መብላት እንዲህ እላለሁ፤ በዚህ ዓለም ጣዖት ከንቱ እንደ ሆነና ከአንዱ ከእግዚአብሔር በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ እናውቃለን። 5መቼም ብዙ አማልክትና ብዙ ጌቶች አሉ፤ በሰማይም ሆነ በምድር አምላክ ተብለው የሚጠሩ አማልክት ቢኖሩም፣ 6ለእኛ ግን ሁሉም ነገር ከእርሱ የሆነ፣ እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ አለን፤ ደግሞም ሁሉም ነገር በእርሱ አማካይነት የሆነ፣ እኛም በእርሱ አማካይነት የሆንን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አለን።

7ነገር ግን ይህን የሚያውቁ ሁሉም አይደሉም፤ አንዳንድ ሰዎች እስከ አሁን ድረስ ጣዖትን ማምለክ ስለ ለመዱ፣ እንዲህ ያለውን ሥጋ ሲበሉ በርግጥ ለጣዖት እንደ ተሠዋ ያስባሉ፤ ኅሊናቸውም ደካማ ስለሆነ ይረክሳል። 8ነገር ግን ምግብ ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላ የሚጐድልብን ነገር የለም፤ ብንበላም የምናተርፈው ነገር አይኖርም።

9ነገር ግን ከነጻነታችሁ የተነሣ የምታደርጉት ለደካሞች ዕንቅፋት እንዳይሆን ተጠንቀቁ። 10አንተ ይህን የመሰለ ዕውቀት ኖሮህ፣ ደካማ ኅሊና ያለው ሰው በቤተ ጣዖት ስትበላ ቢያይህ፣ ለጣዖት የተሠዋውን ምግብ ለመብላት አይደፋፈርምን? 11ስለዚህ ክርስቶስ የሞተለት ይህ ደካማ ወንድም በአንተ ዕውቀት ምክንያት ጠፋ ማለት ነው። 12በዚህ መንገድ ወንድሞቻችሁን በመበደልና ደካማ ኅሊናቸውን በማቍሰል፣ ክርስቶስን ትበድላላችሁ። 13ስለዚህ እኔ የምበላው ነገር ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ፣ ወንድሜን ላለማሰናከል ስል ከቶ ሥጋ አልበላም።

Thai New Contemporary Bible

1โครินธ์ 8:1-13

อาหารที่เซ่นไหว้รูปเคารพ

1เกี่ยวกับอาหารที่เซ่นไหว้รูปเคารพเป็นดังนี้ เรารู้ว่าเราทั้งหลายล้วนมีความรู้8:1 หรืออย่างที่ท่านกล่าวว่า “เราทุกคนล้วนมีความรู้ ความรู้นั้นทำให้ลำพอง แต่ความรักเสริมสร้างขึ้น 2ผู้ใดที่คิดว่าตนเองรู้บางสิ่งแล้ว ผู้นั้นยังไม่รู้อย่างที่เขาควรจะรู้ 3แต่ผู้ที่รักพระเจ้า พระเจ้าก็ทรงรู้จักผู้นั้น

4ดังนั้นแล้วเกี่ยวกับการกินอาหารที่ได้เซ่นไหว้รูปเคารพ เรารู้อยู่ว่ารูปเคารพนั้นไม่มีความหมายอะไรในโลกนี้และมีพระเจ้าแต่เพียงองค์เดียวเท่านั้น 5เพราะถึงแม้ว่าจะมีสิ่งที่เรียกว่าพระเจ้ามากมาย ไม่ว่าในสวรรค์หรือบนแผ่นดินโลก (จริงอยู่ มี “พระ” และ “เจ้า” มากมาย) 6แต่สำหรับพวกเรามีพระเจ้าองค์เดียว คือพระบิดาผู้ทรงเป็นที่มาของสิ่งสารพัด เรามีชีวิตอยู่เพื่อพระองค์ และมีองค์พระผู้เป็นเจ้าองค์เดียวคือพระเยซูคริสต์ สิ่งสารพัดเป็นมาโดยทางพระองค์ และเรามีชีวิตอยู่โดยทางพระองค์

7แต่ไม่ใช่ทุกคนที่รู้เช่นนี้ บางคนยังคุ้นเคยกับรูปเคารพ เมื่อพวกเขากินอาหารนั้นก็ถือว่าเป็นของที่เซ่นไหว้รูปเคารพ และเพราะจิตสำนึกของพวกเขายังอ่อนจึงเป็นมลทิน 8แต่อาหารไม่ได้ทำให้เราเข้าใกล้พระเจ้า ถ้าไม่รับประทานเราก็ไม่แย่ลง ถ้ารับประทานเราก็ไม่ได้ดีขึ้น

9อย่างไรก็ตามจงระวังอย่าให้การกระทำโดยอิสระเสรีของเรากลายเป็นหินสะดุดของพี่น้องที่อ่อนแอ 10เพราะหากผู้ที่จิตสำนึกยังอ่อนเห็นท่านผู้มีความรู้นั่งรับประทานอาหารอยู่ในวิหารของรูปเคารพเหล่านี้ เขาจะไม่ฮึกเหิมรับประทานของที่เซ่นไหว้รูปเคารพบ้างหรือ? 11ดังนั้นกลายเป็นว่าความรู้ของท่านทำลายพี่น้องที่อ่อนแอคนนั้น ทั้งที่พระคริสต์ได้ทรงวายพระชนม์เพื่อเขา 12เมื่อท่านทำบาปต่อพวกพี่น้องเช่นนี้และทำร้ายจิตสำนึกที่อ่อนแอของพวกเขา ท่านก็ทำบาปต่อพระคริสต์ 13ฉะนั้นหากสิ่งที่ข้าพเจ้ารับประทานทำให้พี่น้องตกลงในบาป ข้าพเจ้าจะไม่รับประทานเนื้อสัตว์อีกเลย เพื่อว่าข้าพเจ้าจะไม่เป็นเหตุให้เขาล้มลง