1 ቆሮንቶስ 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 2:1-16

1ወንድሞች ሆይ፤ ወደ እናንተ በመጣሁ ጊዜ፣ የእግዚአብሔርን ምስጢር2፥1 አንዳንድ ቅጆች ስለ እግዚአብሔር ይላሉ በረቀቀ የንግግር ችሎታ ወይም በላቀ ጥበብ ልገልጥላችሁ አልመጣሁም። 2በመካከላችሁ ሳለሁ ኢየሱስ ክርስቶስን ያውም የተሰቀለውን፣ እርሱን ብቻ እንጂ ሌላ እንዳላውቅ ወስኜ ነበርና። 3ወደ እናንተ የመጣሁት በድካምና በፍርሀት፣ እንዲሁም በብዙ መንቀጥቀጥ ነበር። 4ቃሌም ስብከቴም የመንፈስን ኀይል በመግለጥ እንጂ፣ በሚያባብል የጥበብ ቃል አልነበረም፤ 5ይኸውም እምነታችሁ በእግዚአብሔር ኀይል እንጂ በሰው ጥበብ ላይ እንዳይመሠረት ነው።

ከመንፈስ የተገኘ ጥበብ

6በበሰሉ ሰዎች መካከል ግን ጥበብን እንናገራለን፤ ይሁን እንጂ የዚህችን ዓለም ጥበብ ወይም የሚጠፉትን የዚህችን ዓለም ገዦች ጥበብ አይደለም። 7ነገር ግን ተሰውሮ የነበረውን የእግዚአብሔርን ምስጢር ጥበብ ነው፤ ይህም ጥበብ እግዚአብሔር ከዘመናት በፊት ለክብራችን አስቀድሞ የወሰነው ነው። 8ከዚህ ዓለም ገዦች አንዳቸውም ይህን ጥበብ አልተረዱትም፤ ቢረዱትማ ኖሮ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉት ነበር። 9ይሁን እንጂ፣ እንደ ተጻፈው፣

“ዐይን ያላየውን፣

ጆሮ ያልሰማውን፣

የሰውም ልብ ያላሰበውን፣

እግዚአብሔር ለሚወድዱት አዘጋጅቷል፤”

10እግዚአብሔር ግን ይህን በመንፈሱ አማካይነት ለእኛ ገልጦልናል።

መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል። 11በውስጡ ካለው ከራሱ መንፈስ በስተቀር ከሰው መካከል የአንድን ሰው ሐሳብ የሚያውቅ ማን አለ? እንደዚሁም ከእግዚአብሔር መንፈስ በስተቀር፣ የእግዚአብሔርን ሐሳብ የሚያውቅ ማንም የለም። 12ከእግዚአብሔር የሆነውን መንፈስ እንጂ፣ የዓለምን መንፈስ አልተቀበልንምና፤ ይህም እግዚአብሔር በነጻ የሰጠንን እናውቅ ዘንድ ነው። 13እኛ የምንናገረው ይህን ነው፤ ከሰው ጥበብ በተማርነው ቃል ሳይሆን፣ ከመንፈስ በተማርነው ቃል እንናገራለን፤ መንፈሳዊ እውነትንም የምንገልጸው በመንፈሳዊ ቃል ነው።2፥13 ወይም መንፈሳዊ እውነትንም ለመንፈሳዊ ሰው እንገልጻለን 14መንፈሳዊ ያልሆነ ሰው ከእግዚአብሔር መንፈስ የሆነውን ነገር ሊቀበል አይችልም፤ ምክንያቱም እንዲህ ያለው ነገር ለእርሱ ሞኝነት ነው፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለሆነ፣ ሊረዳው አይችልም። 15መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉንም ነገር ይመረምራል፤ ራሱ ግን በማንም አይመረመርም።

16“ያስተምረው ዘንድ፣

የጌታን ልብ ማን ዐወቀው?”

እኛ ግን የክርስቶስ ልብ አለን።

Thai New Contemporary Bible

1โครินธ์ 2:1-16

1พี่น้องทั้งหลาย เมื่อข้าพเจ้ามาหาท่าน ข้าพเจ้าไม่ได้มาด้วยคำพูดสละสลวยหรือสติปัญญาเลอเลิศ ขณะที่ข้าพเจ้าประกาศคำพยานเกี่ยวกับพระเจ้า2:1 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าประกาศข้อความล้ำลึกของพระเจ้าให้แก่ท่าน 2เพราะข้าพเจ้าตั้งใจไว้ว่าขณะอยู่กับท่าน ข้าพเจ้าจะไม่รู้อะไรอื่นเลยนอกจากเรื่องพระเยซูคริสต์และการที่พระองค์ทรงถูกตรึงตายบนไม้กางเขน 3ข้าพเจ้ามาหาท่านด้วยความอ่อนแอกับความกลัวจนตัวสั่นอย่างมาก 4คำพูดและคำเทศนาของข้าพเจ้าไม่ใช่ถ้อยคำโน้มน้าวใจด้วยสติปัญญา แต่เป็นการสำแดงถึงฤทธิ์อำนาจของพระวิญญาณ 5เพื่อว่าความเชื่อของท่านจะไม่อาศัยสติปัญญาของมนุษย์ แต่พึ่งฤทธิ์อำนาจของพระเจ้า

สติปัญญาจากพระวิญญาณ

6อย่างไรก็ดีพวกเรากล่าวถ้อยคำแห่งสติปัญญากับบรรดาผู้ที่เป็นผู้ใหญ่แล้ว แต่ไม่ใช่สติปัญญาของยุคนี้หรือสติปัญญาของผู้ครอบครองของยุคนี้ผู้ซึ่งกำลังจะเสื่อมสูญไป 7แต่พูดถึงพระปัญญาอันล้ำลึกของพระเจ้า พระปัญญาซึ่งทรงปิดบังและซึ่งพระเจ้าทรงกำหนดไว้เพื่อศักดิ์ศรีของเราตั้งแต่ก่อนเริ่มสร้างโลก 8ไม่มีผู้ครอบครองคนใดของยุคนี้ที่เข้าใจพระปัญญา เพราะหากเข้าใจ ย่อมจะไม่ตรึงองค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงพระเกียรติสิริไว้ที่ไม้กางเขน 9ตามที่มีเขียนไว้ว่า

“ไม่เคยมีใครได้เห็น

ไม่เคยมีใครได้ยิน

ไม่เคยมีจิตใจใดหยั่งรู้

สิ่งที่พระเจ้าทรงเตรียมไว้ให้บรรดาผู้ที่รักพระองค์”2:9 อสย.64:4

10แต่พระเจ้าได้ทรงเปิดเผยสิ่งนั้นแก่เราโดยพระวิญญาณของพระองค์

พระวิญญาณทรงสืบทราบทุกสิ่งแม้แต่สิ่งล้ำลึกของพระเจ้า 11ความคิดของมนุษย์ใครไหนเล่าจะรู้เว้นแต่จิตวิญญาณของคนนั้นเอง? เช่นเดียวกันไม่มีใครหยั่งรู้พระดำริของพระเจ้าได้นอกจากพระวิญญาณของพระเจ้า 12เราไม่ได้รับวิญญาณของโลก แต่รับพระวิญญาณซึ่งมาจากพระเจ้า เพื่อเราจะเข้าใจสิ่งที่พระเจ้าประทานแก่เราอย่างไม่จำกัด 13นี่คือสิ่งที่พวกเราพูด ไม่ใช่ด้วยถ้อยคำซึ่งสติปัญญาของมนุษย์สอนไว้ แต่ด้วยถ้อยคำซึ่งพระวิญญาณทรงสอน เป็นการสำแดงความจริงด้านจิตวิญญาณด้วยถ้อยคำฝ่ายจิตวิญญาณ2:13 หรือเป็นการแปลความจริงด้านจิตวิญญาณแก่ผู้อยู่ฝ่ายจิตวิญญาณ 14ผู้ปราศจากพระวิญญาณไม่อาจรับสิ่งที่มาจากพระวิญญาณของพระเจ้าเพราะเห็นเป็นเรื่องโง่เขลา และเขาไม่สามารถเข้าใจสิ่งเหล่านั้นเพราะต้องอาศัยการแยกแยะฝ่ายจิตวิญญาณจึงจะเข้าใจสิ่งเหล่านั้นได้ 15ผู้ที่อยู่ฝ่ายจิตวิญญาณวินิจฉัยทุกสิ่งได้ แต่ตัวเขาเองไม่ตกอยู่ในการวินิจฉัยของใคร

16“เพราะใครเล่าจะหยั่งรู้พระทัยขององค์พระผู้เป็นเจ้า

ที่จะสั่งสอนพระองค์ได้?”2:16 อสย.40:13

แต่เรามีพระทัยของพระคริสต์