1 ሳሙኤል 25 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 25:1-44

ዳዊት፣ ናባልና አቢግያ

1ሳሙኤልም ሞተ፤ እስራኤል ሁሉ ተሰብስበው አለቀሱለት፤ አርማቴም ባለው ቤቱም ቀበሩት።

ከዚያም ዳዊት ተነሥቶ ወደ ማዖን ምድረ በዳ ወረደ። 2በማዖን ምድር በቀርሜሎስ ንብረት ያለው አንድ ባለጠጋ ሰው ነበረ፤ እርሱም አንድ ሺሕ ፍየሎችና በቀርሜሎስ የሚሸልታቸው ሦስት ሺሕ በጎች ነበሩት። 3የሰውየው ስም ናባል፣ የሚስቱም ስም አቢግያ ነበረ። እርሷም አስተዋይና ውብ ነበረች፤ ባሏ ግን ባለጌና ምግባረ ብልሹ ሰው ነበረ፤ እርሱም ከካሌብ ወገን ነበር።

4ዳዊት በምድረ በዳ ሳለ ናባል በጎቹን እንደሚሸልት ሰማ። 5እርሱም ዐሥር ወጣቶችን እንዲህ ሲል ላካቸው፤ “ወደ ቀርሜሎስ ወደ ናባል ውጡ፤ በስሜም ሰላምታ አቅርቡለት። 6እንዲህም በሉት፤ ‘ዕድሜህ ይርዘም! ሰላም ለአንተ ይሁን፤ ሰላም ለቤተ ሰብህና የአንተ ለሆነው ሁሉ ይሁን።

7“ ‘በዚህ ጊዜ በጎች እንደምትሸልት ሰምቻለሁ፤ እረኞችህ ከእኛ ጋር በነበሩበት ጊዜ፣ ያደረስንባቸው ጕዳት የለም፤ ቀርሜሎስ በነበሩበት ጊዜ ሁሉ፣ የጠፋባቸው አንዳች ነገር አልነበረም። 8የገዛ አገልጋዮችህን ጠይቅ፤ እነርሱም ይነግሩሃል። ስለዚህ አመጣጣችን በጥሩ ቀን በመሆኑ፣ እነዚህ ወጣቶቼ በፊትህ ሞገስ ያግኙ። እባክህን ለአገልጋዮችህና ለልጅህ ለዳዊት የምትችለውን ያህል ስጥ።’ ”

9የዳዊት ሰዎች ከዚያ እንደ ደረሱም፣ በዳዊት ስም ይህንኑ መልእክት ለናባል ከተናገሩ በኋላ ምላሹን ይጠባበቁ ጀመር።

10ናባልም ለዳዊት አገልጋዮች እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ለመሆኑ ይህ ዳዊት ማነው? የእሴይስ ልጅ ማን ነው? በአሁኑ ጊዜ ከጌቶቻቸው የሚኰበልሉ አገልጋዮች ብዙ ናቸው። 11ታዲያ እንጀራዬንና ውሃዬን እንዲሁም በጎቼን ለሚሸልቱልኝ ሰዎች ያረድሁትን ፍሪዳ ከየት እንደ መጡ ለማይታወቁ ሰዎች የምሰጠውስ ለምንድን ነው?”

12የዳዊት ሰዎችም ወደ መጡበት ተመለሱ፤ እዚያም እንደ ደረሱ የተባሉትን ሁሉ ነገሩት። 13ዳዊትም ሰዎቹን፣ “በሉ ሁላችሁም ሰይፋችሁን ታጠቁ” አላቸው። ስለዚህ ሁሉም ሰይፋቸውን ታጠቁ፤ ዳዊትም የራሱን ታጠቀ። አራት መቶ ያህል ሰዎች ከዳዊት ጋር ሲወጡ መቶ ያህሉ ግን ጓዝ ለመጠበቅ ቀሩ።

14ከአገልጋዮቹ አንዱ ለናባል ሚስት ለአቢግያ እንዲህ አላት፤ “እነሆ፤ ዳዊት ሰላምታውን እንዲያቀርቡለት ከምድረ በዳ ወደ ጌታችን መልእክተኞች ልኮ ነበር፤ እርሱ ግን የስድብ ናዳ አወረደባቸው። 15እነዚህ ሰዎች ግን እጅግ መልካም ነበሩ፤ ጕዳትም አላደረሱብንም፤ በዱር አብረናቸው በነበርንበት ጊዜም ሁሉ፣ ምንም ነገር አልጠፋብንም። 16በጎቻችንን እየጠበቅን አብረናቸው ባሳለፍነው ጊዜ ሁሉ፣ ቀንም ሆነ ሌሊት በዙሪያችን ዐጥር ሆነውን ነበር። 17አሁንም በጌታችንና በመላው ቤተ ሰቡ ላይ መከራ እያንዣበበ ስለሆነ፣ አስቢበትና የምታደርጊውን አድርጊ፤ እርሱ እንደ ሆነ እንዲህ ያለ ባለጌ ሰው ስለሆነ፣ ደፍሮ የሚነግረው አንድም ሰው የለም።”

18አቢግያም ጊዜ አላጠፋችም፤ ሁለት መቶ እንጀራ፣ ሁለት አቍማዳ የወይን ጠጅ፣ አምስት የተሰናዱ በጎች፣ አምስት መስፈሪያ25፥18 37 ሊትር ያህል ነው። የተጠበሰጠ እሸት፣ መቶ የወይን ዘለላና ዘቢብ፣ ሁለት መቶ ጥፍጥፍ የበለስ ፍሬ ወስዳ በአህዮች ላይ ጫነች። 19ከዚያም አገልጋዮቿን፣ “ቀድማችሁኝ ሂዱ፤ እኔም እከተላችኋለሁ” አለቻቸው፤ ለባሏ ለናባል ግን አልነገረችውም።

20እርሷም በአህያዋ ላይ ተቀምጣ ወደ ሸለቆው በምትወርድበት ጊዜ ዳዊትና ሰዎቹ ወደ እርሷ ወረዱ፤ እርሷም አገኘቻቸው። 21ዳዊትም እንዲህ ብሎ ነበር፤ “ምንም ነገር እንዳይጠፋበት የዚህን ሰው ሀብት በምድረ በዳ ያን ያህል መጠበቄ ለካ በከንቱ ኖሯል፤ ደግ በሠራሁ ይኸው ክፉ መለሰልኝ። 22ነገ ጧት የእርሱ ከሆነው ሁሉ አንድ ወንድ እንኳ በሕይወት ባስቀር እግዚአብሔር በዳዊት ላይ25፥22 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን በዳዊት ጠላቶች ላይ ይላል። እንዲህ ያለውን ነገር ያድርግበት፣ ከዚህም የከፋ ይጨምርበት!”

23አቢግያም ዳዊትን ባየች ጊዜ ወዲያው ከአህያዋ ወርዳ፣ በዳዊትም ፊት በግምባሯ ተደፍታ እጅ ነሣች። 24በእግሩም ላይ ወድቃ እንዲህ አለች፤ “ጌታዬ ሆይ፤ በደሉ በእኔ ላይ ብቻ ይሁን፤ እባክህ አገልጋይህ ታናግርህ፤ የምትልህንም ስማ። 25ጌታዬ፣ ያን ባለጌ ሰው ናባልን ከቁም ነገር አይቍጠረው፤ ስሙ ራሱ ጅል ማለት ስለሆነ፣ ሰውየውም ልክ እንደ ስሙ ነው፤ ጅልነትም አብሮት የኖረ ነው። እኔ አገልጋይህ ግን ጌታዬ የላካቸውን ጕልማሶች አላየኋቸውም። 26ጌታዬ ሆይ፤ ሕያው እግዚአብሔርን! በሕያው ነፍስህም እምላለሁ፤ ደም ከማፍሰስና በገዛ እጅህ ከመበቀል የጠበቀህ እግዚአብሔር ነው፤ አሁንም ጠላቶችህና ጌታዬን ሊጐዱ የሚፈልጉ ሁሉ እንደ ናባል ይሁኑ፤ 27አገልጋይህም ለጌታዬ ያመጣችው ይህ ስጦታ አንተን ለሚከተሉ ጕልማሶች ይሰጥ። 28ጌታዬ የእግዚአብሔርን ጦርነት ስለሚዋጋ እግዚአብሔርም ለጌታዬ ሥርወ መንግሥቱን በርግጥ ለዘላለም የሚያጸናለት በመሆኑ፣ እባክህ የእኔን የአገልጋይህን በደል ይቅር በል፤ በሕይወት ዘመንህም ሁሉ ክፋት አይገኝብህ። 29ማንም ሰው ሕይወትህን ለማጥፋት ቢያሳድድህ እንኳ፣ የጌታዬ ሕይወት በሕያዋን አንድነት እስራት ውስጥ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ በሰላም ትጠበቃለች፤ የጠላቶችህን ሕይወት ግን፣ እንደ ወንጭፍ ድንጋይ ይወነጭፋል። 30እግዚአብሔር ለጌታዬ በሰጠው ተስፋ መሠረት በጎውን ነገር ሁሉ ባደረገለትና በእስራኤልም ላይ ባነገሠው ጊዜ፣ 31ጌታዬ የምታዝንበት ምክንያት ወይም የኅሊና ጸጸት አይኖርህም፤ በከንቱ ያፈሰስኸውም ደም ሆነ በገዛ እጅህ የተበቀልኸው የለምና። እግዚአብሔር በጎ ነገር ባደረገልህ ጊዜ እኔን አገልጋይህን ዐስበኝ።”

32ዳዊትም አቢግያን እንዲህ አላት፤ “ዛሬ እንድታገኚኝ ወደ እኔ የላከሽ፣ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። 33ደም እንዳላፈስና በገዛ እጄ እንዳልበቀል ዛሬ ስለ ጠበቅሽኝ ስለ በጎ ሐሳብሽ አንቺም የተባረክሽ ሁኚ። 34ጕዳት እንዳላደርስብሽ የጠበቀኝ የእስራኤል አምላክ ሕያው እግዚአብሔርን! እንዲህ በቶሎ መጥተሽ ባታገኚኝ ኖሮ፣ እስኪነጋ ድረስ ለናባል አንድ ወንድ እንኳ ባልተረፈ ነበር።”

35ከዚያም ዳዊት ያመጣችለትን ከእጇ ተቀብሎ፣ “በሰላም ወደ ቤትሽ ሂጂ፤ እነሆ፤ ቃልሽን ሰምቻለሁ፤ የጠየቅሽኝንም ተቀብያአለሁ” አላት።

36አቢግያም ወደ ናባል በተመለሰች ጊዜ፣ እነሆ፤ በቤቱ እንደ ንጉሥ ግብዣ ትልቅ ግብዣ አድርጎ አገኘችው፤ ክፉኛም ሰክሮ ልቡ በደስታ ተሞልቶ ነበር። ስለዚህ እስኪነጋ ድረስ ምንም አልነገረችውም። 37ነግቶ የወይን ጠጁ ስካር ካለፈለት በኋላ የሆነውን ሁሉ ስትነግረው ልቡ ቀጥ አለ፤ ሰውነቱም እንደ ድንጋይ በድን ሆነ። 38ዐሥር ቀን ያህል ካለፈ በኋላ፣ እግዚአብሔር ናባልን ቀሠፈው፤ እርሱም ሞተ።

39ዳዊትም ናባል መሞቱን በሰማ ጊዜ፣ “የናባልን ስድብ የተበቀለልኝና እኔን አገልጋዩን ክፉ ከማድረግ የጠበቀኝ እግዚአብሔር ይመስገን፤ ናባል የሠራውንም ክፉ ነገር በራሱ ላይ መለሰበት” አለ።

ዳዊትም አቢግያ ሚስት ትሆነው ዘንድ በመጠየቅ መልእክት ላከባት። 40አገልጋዮቹም ወደ ቀርሜሎስ ሄደው አቢግያን፣ “ሚስት ትሆኚው ዘንድ እንድንወስድሽ ዳዊት ወደ አንቺ ልኮናል” አሏት።

41እርሷም ተነሥታ በግምባሯ በመደፋት እጅ ከነሣች በኋላ፣ “እነሆ፤ እኔ ገረድህ አንተን ለማገልገል፣ የጌታዬንም አገልጋዮች እግር ለማጠብ ዝግጁ ነኝ” አለች። 42አቢግያም ወዲያውኑ በአህያ ላይ ተቀምጣ አምስት አገልጋዮቿን በማስከተል፣ ከዳዊት መልእክተኞች ጋር ሄደች፤ ለዳዊትም ሚስት ሆነችው። 43እንዲሁም ዳዊት ኢይዝራኤላዊቷን አኪናሆምን አገባ፣ ሁለቱም ሚስቶቹ ሆኑ። 44ሳኦል ግን የዳዊት ሚስት የነበረችውን ልጁን ሜልኮልን፣ ለጋሊም ተወላጅ ለሌሳ ልጅ ለፈልጢ ሰጥቶ ነበር።

Thai New Contemporary Bible

1ซามูเอล 25:1-44

ดาวิด นาบาล และอาบีกายิล

1ซามูเอลสิ้นชีวิตลง ชาวอิสราเอลทั้งปวงพากันมาร่วมชุมนุมไว้อาลัยให้แก่ซามูเอล และฝังศพเขาที่รามาห์บ้านเกิดของเขา

ส่วนดาวิดย้ายไปที่ถิ่นกันดารมาโอน25:1 ภาษาฮีบรูว่าปาราน 2มีเศรษฐีคนหนึ่งในมาโอน มีทรัพย์สินอยู่ที่คารเมล เขามีแพะหนึ่งพันตัว แกะสามพันตัว ขณะนั้นเขาไปที่คารเมลเพื่อตัดขนแกะ 3เศรษฐีผู้นี้มีนามว่านาบาล เป็นวงศ์วานของคาเลบ ภรรยาของเขาชื่ออาบีกายิล เป็นคนสวยและเฉลียวฉลาด แต่ตัวนาบาลเป็นคนใจแคบและหยาบคาย

4ขณะที่ดาวิดอยู่ในถิ่นกันดาร เขาได้ยินว่านาบาลกำลังตัดขนแกะ 5ก็สั่งชายหนุ่มสิบคนว่า “จงไปหานาบาลที่คารเมลและทักทายเขาในนามของเรา 6และแจ้งเขาว่า ‘ขอให้ท่านมีอายุมั่นขวัญยืน! ขอให้ท่านและครอบครัวมีสุขภาพดี! ขอให้ทุกอย่างในกรรมสิทธิ์ของท่านเจริญขึ้น!

7“ ‘ข้าพเจ้าทราบมาว่าท่านกำลังตัดขนแกะ เราไม่เคยทำร้ายคนเลี้ยงแกะของท่านเลยขณะที่พวกเขาอาศัยอยู่ท่ามกลางพวกเรา ตลอดเวลาที่พวกเขาอยู่ในคารเมลก็ไม่มีสิ่งใดขาดหายไป 8โปรดถามคนของท่านดูว่าเป็นอย่างที่กล่าวมานี้หรือไม่ ฉะนั้นขอท่านเกื้อหนุนแก่คนของข้าพเจ้าเพราะเรามาเยือนในงานเลี้ยงฉลองนี้ โปรดให้ดาวิดบุตรและผู้รับใช้ของท่านตามแต่จะเอื้อเฟื้อ’”

9เมื่อบรรดาคนของดาวิดมาถึง ก็เรียนให้นาบาลทราบตามนั้นในนามของดาวิดและรอฟังคำตอบ

10นาบาลตอบคนรับใช้ของดาวิดว่า “ดาวิดเป็นใครกัน? ลูกเจสซีคนนี้เป็นใครกัน? ทุกวันนี้มีลูกจ้างมากมายหนีนายของตัวไป 11ควรหรือที่เราจะเอาขนมปัง น้ำ และเนื้อที่เราฆ่าสำหรับคนตัดขนแกะของเราไปให้กลุ่มคนที่เราไม่รู้จักหัวนอนปลายเท้า?”

12คนของดาวิดจึงกลับมารายงานทุกถ้อยคำที่นาบาลกล่าว 13ดาวิดสั่งว่า “ให้ทุกคนคาดดาบ!” ตัวดาวิดเองก็สะพายดาบออกเดินทาง มีพรรคพวกสี่ร้อยคนติดตามไป ส่วนอีกสองร้อยคนเฝ้าสัมภาระอยู่ที่กองหลัง

14มีคนใช้คนหนึ่งของนาบาลไปบอกอาบีกายิลภรรยาของนาบาลว่า “ดาวิดส่งคนจากถิ่นกันดารมาทักทายนายท่าน แต่นายท่านไปดูถูกเอ็ดตะโรพวกนั้น 15แท้ที่จริงคนของดาวิดดีต่อเรามาก พวกเขาไม่เคยทำอันตรายอะไรเราเลย ตลอดเวลาที่เราอยู่กลางทุ่งใกล้ๆ พวกเขา ไม่มีอะไรหายสักอย่าง 16พวกเขาเป็นเกราะกำบังให้เราทั้งกลางวันและกลางคืนตลอดเวลาที่เราเลี้ยงแกะอยู่ใกล้ๆ พวกเขา 17ขอให้นายหญิงตรึกตรองดูว่าจะทำอะไรได้บ้าง เพราะภัยกำลังจะมาถึงนายท่านและครอบครัว นายท่านเป็นคนชั่วร้ายไม่ยอมฟังคำทัดทานจากใครเลย”

18อาบีกายิลไม่รอช้า รีบจัดขนมปังสองร้อยก้อน เหล้าองุ่นสองถุงหนัง เนื้อแกะที่ทำเสร็จแล้วห้าตัว ข้าวคั่วประมาณ 37 ลิตร25:18 ภาษาฮีบรูว่า5 ซีห์ ขนมลูกเกดหนึ่งร้อยก้อน มะเดื่ออัดสองร้อยก้อน และใช้ลาบรรทุกของเหล่านี้ไป 19นางสั่งคนรับใช้ว่า “รีบล่วงหน้าไปก่อน เดี๋ยวฉันจะตามไป” แต่นางไม่ได้บอกนาบาลสามีของนาง

20ขณะที่นางขี่ลามาตามทางสู่หุบเขาลึก ก็พบดาวิดกับพวกสวนทางมา 21ดาวิดเพิ่งกล่าวว่า “เปล่าประโยชน์ที่เราเฝ้าดูแลฝูงสัตว์ของเจ้าคนนี้ในถิ่นกันดาร ไม่ให้อะไรหายไปสักอย่าง เขากลับทำชั่วตอบแทนการดีของเรา 22หากถึงรุ่งเช้าแล้ว เรายังไว้ชีวิตผู้ชายที่เป็นคนของนาบาลแม้แต่คนเดียว ขอพระเจ้าทรงจัดการกับเรา25:22 ภาษาฮีบรูว่ากับศัตรูของดาวิดอย่างสาหัสสากรรจ์!”

23เมื่ออาบีกายิลเห็นดาวิด นางรีบลงจากหลังลา หมอบกราบซบหน้าลงกับพื้นต่อหน้าดาวิด 24นางหมอบลงแทบเท้าดาวิดและกล่าวว่า “นายท่านเจ้าข้า ดิฉันขอน้อมรับคำตำหนิทั้งหมด ขอให้ผู้รับใช้ของท่านได้พูดกับท่าน ขอโปรดฟังสิ่งที่ผู้รับใช้จะพูด 25ขอนายท่านอย่าสนใจนาบาลคนชั่วร้ายนั้นเลย เขาเป็นคนโง่สมชื่อและความเขลาคงจะติดตามเขาไป ส่วนดิฉันผู้รับใช้ของท่านไม่ทันได้พบคนที่นายท่านส่งไป 26นายท่านเจ้าข้า เนื่องจากองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงป้องกันไม่ให้มือของนายท่านเปื้อนเลือดด้วยการลงมือแก้แค้นเอง องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใดและท่านมีชีวิตอยู่แน่ฉันใด ขอให้ศัตรูและคนทั้งปวงที่มุ่งร้ายต่อนายท่านจงเป็นเหมือนนาบาลฉันนั้น 27และนี่คือของกำนัลที่ผู้รับใช้ของนายท่านนำมามอบให้ท่านกับคนของท่าน

28“โปรดยกโทษให้แก่การละเมิดของผู้รับใช้ของท่านด้วย เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงให้ราชวงศ์ของนายท่านยืนยงตลอดไปอย่างแน่นอน เพราะท่านได้ต่อสู้ในสงครามขององค์พระผู้เป็นเจ้าขออย่าให้พบการกระทำผิดในตัวท่านเลยตลอดชีวิตของท่าน 29ถึงแม้จะมีคนไล่ล่าเอาชีวิตของท่าน นายท่านก็ยังคงปลอดภัยอยู่ภายใต้การปกป้องคุ้มครองของพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน แต่ชีวิตศัตรูของท่านจะลับหายไปเหมือนถูกเหวี่ยงจากสลิง 30เมื่อองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบันดาลสิ่งดีงามทั้งปวงแก่นายท่านตามพระสัญญา และทรงตั้งท่านเป็นผู้นำเหนืออิสราเอลแล้ว 31นายท่านจะได้ไม่ต้องเสียใจที่ฆ่าคนโดยไม่จำเป็นหรือลงมือแก้แค้นเอง และเมื่อองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบันดาลความสำเร็จแก่นายท่านแล้ว โปรดระลึกถึงผู้รับใช้ของท่านด้วย”

32ดาวิดตอบอาบีกายิลว่า “ขอถวายสรรเสริญแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลผู้ทรงส่งเจ้ามาพบเราในวันนี้ 33ขอพระเจ้าอวยพรเจ้าสำหรับการตัดสินใจที่ดีของเจ้าและที่เจ้าช่วยป้องกันเราไม่ให้ฆ่าคนในวันนี้ ไม่ต้องแก้แค้นให้มือเปื้อนเลือด 34มิฉะนั้นพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลผู้ทรงป้องกันไม่ให้เราทำอันตรายเจ้า ทรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด หากเจ้าไม่ได้มาพบเราอย่างรวดเร็ว คนของนาบาลคงไม่มีชีวิตเหลือรอดแม้แต่คนเดียวในเช้าวันพรุ่งนี้ฉันนั้น”

35แล้วดาวิดจึงรับของกำนัลจากนาง และกล่าวว่า “จงกลับบ้านไปโดยสวัสดิภาพเถิด เรารับฟังและจะทำตามคำขอร้องของเจ้า”

36เมื่อนางกลับมาถึงบ้าน ก็พบว่านาบาลได้จัดงานเลี้ยงใหญ่ราวกับงานเลี้ยงของกษัตริย์ เขากำลังเมาอย่างหนัก นางจึงไม่ได้เล่าสิ่งใดให้เขาฟังจนกระทั่งเช้าวันรุ่งขึ้น 37เมื่อเขาสร่างเมาแล้ว และภรรยาเล่าเหตุการณ์ทุกอย่างที่เกิดขึ้นให้ฟัง เขาถึงกับตกใจมากและแน่นิ่งไปเหมือนก้อนหิน 38ประมาณสิบวันหลังจากนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงลงโทษนาบาลและเขาก็ตาย

39เมื่อดาวิดได้ยินว่านาบาลตายแล้ว ก็กล่าวว่า “สรรเสริญองค์พระผู้เป็นเจ้าพระองค์ทรงให้ความเป็นธรรมแก่เราแล้วที่นาบาลดูหมิ่นเรา และทรงป้องกันผู้รับใช้ของพระองค์ไม่ให้ทำผิด และทรงให้นาบาลได้รับโทษสาสมกับความผิดแล้ว”

จากนั้นดาวิดก็ส่งคนไปขอนางอาบีกายิลมาเป็นภรรยา 40คนของดาวิดมาที่คารเมล และกล่าวกับอาบีกายิลว่า “ดาวิดส่งเรามารับท่านไปเป็นภรรยาของเขา”

41นางหมอบกราบซบหน้าลงกับพื้นกล่าวว่า “ผู้รับใช้ของท่านอยู่นี่แล้ว พร้อมที่จะรับใช้ท่าน และล้างเท้าให้บริวารของนายท่าน” 42อาบีกายิลรีบขึ้นลาไปกับผู้สื่อสารของดาวิด โดยมีสาวใช้ห้าคนติดตามไปด้วย นางได้เป็นภรรยาของดาวิด 43ดาวิดยังได้แต่งงานกับนางอาหิโนอัมจากยิสเรเอลด้วย และนางทั้งสองได้เป็นภรรยาของดาวิด 44แต่ซาอูลทรงยกมีคาลราชธิดาของพระองค์ซึ่งเป็นภรรยาของดาวิดให้แก่ปัลทีเอล25:44 ภาษาฮีบรูว่าปัลทีเป็นอีกรูปหนึ่งของปัลทีเอลบุตรลาอิชผู้มาจากกัลลิม