1 ሳሙኤል 1 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 1:1-28

የሳሙኤል መወለድ

1በተራራማው በኤፍሬም አገር በአርማቴም መሴፋ የሚኖር ሕልቃና የተባለ አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም ኤፍሬማዊ ሲሆን፣ የኤያሬምኤል ልጅ፣ የኢሊዩ ልጅ፣ የቶሑ ልጅ፣ የናሲብ ልጅ፣ ነበረ። 2እርሱም አንዲቱ ሐና፣ ሌላዪቱ ፍናና የተባሉ ሁለት ሚስቶች ነበሩት፤ ፍናና ልጆች ሲኖሯት፣ ሐና ግን ምንም ልጅ አልነበራትም።

3ያም ሰው ሁሉን ቻይ ለሆነው ለእግዚአብሔር ለመስገድና መሥዋዕት ለመሠዋት በየዓመቱ ከሚኖርበት ከተማ ወደ ሴሎ ይወጣ ነበር። በዚያም ሁለቱ የዔሊ ልጆች አፍኒንና ፊንሐስ የእግዚአብሔር ካህናት ነበሩ። 4ሕልቃና ወደ ሴሎ ሄዶ መሥዋዕት የሚሠዋበት ወቅት በደረሰ ጊዜ ሁሉ፣ ለሚስቱ ለፍናና እንዲሁም ለወንዶችና ለሴቶች ልጆቿ ሁሉ ከሥጋው ድርሻቸውን ይሰጣቸው ነበር። 5ሐናን ግን ይወድዳት ስለ ነበር፣ ዕጥፍ ድርሻ ይሰጣት ነበር፤ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ማሕፀኗን ዘግቶት ነበር። 6እግዚአብሔር ማሕፀኗን ስለ ዘጋም ጣውንቷ ታስቈጣት፣ ታበሳጫትም ነበር። 7ይህም በየዓመቱ ይደጋገም ነበር፤ ሐና ወደ እግዚአብሔር ቤት በምትወጣበት ጊዜ ሁሉ፣ እስክታለቅስና መብላት እስኪያቅታት ድረስ ጣውንቷ ታበሳጫት ነበር። 8ባሏ ሕልቃናም እርሷን፣ “ሐና ሆይ፤ ለምን ታለቅሻለሽ? ለምንስ አትበዪም? ልብሽስ ለምን ያዝናል? ከዐሥር ወንዶች ልጆች እኔ አልበልጥብሽምን?” ይላት ነበር።

9አንድ ጊዜ በሴሎ ሳሉ ከበሉና ከጠጡ በኋላ ሐና ተነሥታ ቆመች፤ በዚያ ጊዜ ካህኑ ዔሊ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ1፥9 የማደሪያ ድንኳን ማለት ነው። መቃን አጠገብ በወንበር ላይ ተቀምጦ ነበር። 10ሐናም በነፍሷ ተመርራ አብዝታ በማልቀስ ወደ እግዚአብሔር ጸለየች። 11እንዲህም ብላ ስእለት ተሳለች፤ “የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ የአገልጋይህን መዋረድ ተመልክተህ ብታስበኝና አገልጋይህን ሳትረሳት ወንድ ልጅ ብትሰጣት፣ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለእግዚአብሔር እሰጠዋለሁ፤ ምላጭም በራሱ ላይ አይደርስም።”

12ሐና ባለማቋረጥ ወደ እግዚአብሔር በጸለየች ጊዜ፣ ዔሊ አፏን ይመለከት ነበር። 13እርሷም በልቧ ትጸልይ ስለ ነበር፤ ከንፈሯ ይንቀሳቀስ እንጂ ድምፅዋ አይሰማም ነበር፤ ዔሊም እንደ ሰከረች አድርጎ ቈጠራት። 14እርሱም “ስካሩ የማይለቅሽ እስከ መቼ ድረስ ነው? የወይን ጠጅሽን ከአንቺ አስወግጂው” አላት።

15ሐናም እንዲህ ብላ መለሰችለት፤ “ጌታዬ ሆይ፤ ሰክሬ አይደለም፤ እኔ ልቧ ክፉኛ የታወከባት ሴት ነኝ፤ ልቤን በእግዚአብሔር ፊት አፈሰስሁ እንጂ፣ የወይን ጠጅም ሆነ ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አልጠጣሁም። 16ይህን ያህል ጊዜ የጸለይሁት ከባድ ከሆነው ጭንቀቴና ሐዘኔ የተነሣ ስለሆነ፣ አገልጋይህን እንደ ምናምንቴ ሴት አትቍጠረኝ።”

17ዔሊም፣ “በሰላም ሂጂ፤ የእስራኤል አምላክ የለመንሽውን ይስጥሽ” ሲል መለሰላት።

18እርሷም፣ “አገልጋይህ በፊትህ ሞገስ ታግኝ” አለች፤ ከዚያም መንገዷን ሄደች፤ ምግብም በላች፤ ከዚያም በኋላ በፊቷ ላይ ሐዘን አልታየም።

19በማግስቱም ጧት ተነሥተው በእግዚአብሔር ፊት ሰገዱ፤ ከዚያም በራማ ወደሚገኘው ቤታቸው ሄዱ። ሕልቃና ከሚስቱ ከሐና ጋር ተኛ፤ እግዚአብሔርም ዐሰባት፤ 20ስለዚህ ሐና ፀነሰች፤ የእርግዝናዋ ወራት በተፈጸመ ጊዜም ወንድ ልጅ ወለደች፤ ስሙንም፤ “ከእግዚአብሔር ለምኜዋለሁ” ስትል ሳሙኤል1፥20 በዕብራይስጡ ሳሙኤል የሚለው ቃል ድምፅ እግዚአብሔር ሰማ ከሚለው ሐረግ ጋር ይመሳሰላል። አለችው።

ሐና ሳሙኤልን ለእግዚአብሔር ሰጠች

21ሰውየውም ሕልቃና ለእግዚአብሔር ዓመታዊውን መሥዋዕት ለመሠዋት ስእለቱን ለማድረስ ቤተ ሰቡን ሁሉ ይዞ ወደ ሴሎ ወጣ። 22ሐና ግን አልሄደችም፤ እርሷም ባሏን፣ “ሕፃኑ ጡት ከተወ በኋላ፣ ወስጄ በእግዚአብሔር ፊት አቀርበዋለሁ፤ እስከ ሕይወቱ ፍጻሜም በዚያ ይኖራል” አለችው።

23ባሏ ሕልቃናም፣ “መልካም መስሎ የታየሽን አድርጊ፤ ጡት እስክታስጥዪው ድረስ እዚሁ ቈዪ፤ ብቻ እግዚአብሔር ቃሉን1፥23 የሙት ባሕር ጥቅልል፣ የሰብዓ ሊቃናትና የሱርስቱ ትርጕም ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን ቃልሽን ይላል። ያጽናልሽ” አላት። ስለዚህ ሐና ሕፃኑን ጡት እስክታስጥለው ድረስ እያጠባችው በቤቷ ተቀመጠች።

24ልጁ ጡት በተወ ጊዜ ከእርሱ ጋር አንድ የሦስት ዓመት ወይፈን1፥24 የሙት ባሕር ጥቅልል፤ የሰብዓ ሊቃናትና የሱርቱ ትርጕም ከዚህ፤ ጋር ይስማማል የማስሬቱ ቅጅ ግን ሦስት ወይፈን ይላል።፣ አንድ የኢፍ መስፈሪያ1፥24 22 ሊትር ያህል ነው። ዱቄትና አንድ አቍማዳ የወይን ጠጅ ወስዳ፣ በሴሎ ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ቤት አመጣችው፣ ልጁም ገና ሕፃን ነበረ። 25ወይፈኑን ካረዱ በኋላም ልጁን ወደ ዔሊ አቀረቡት። 26ሐናም ዔሊን እንዲህ አለችው፤ “ጌታዬ ሆይ፤ በነፍስህ እምላለሁ፤ እዚህ ቦታ ላይ በአጠገብህ ቆማ ወደ እግዚአብሔር ስትጸልይ የነበረች ያች ሴት እኔ ነኝ። 27ይህን ልጅ እንዲሰጠኝ ጸለይሁ፤ እግዚአብሔርም የለመንሁትን ሰጠኝ። 28ስለዚህ እኔም ለእግዚአብሔር እሰጠዋለሁ፤ በሕይወት ዘመኑም ሁሉ ለእግዚአብሔር የተሰጠ ይሆናል።” እርሱም በዚያ ለእግዚአብሔር ሰገደ።

New International Reader’s Version

1 Samuel 1:1-28

Samuel Is Born

1A certain man from Ramathaim in the hill country of Ephraim was named Elkanah. He was the son of Jeroham. Jeroham was the son of Elihu. Elihu was the son of Tohu. Tohu was the son of Zuph. Elkanah belonged to the family line of Zuph. Elkanah lived in the territory of Ephraim. 2Elkanah had two wives. One was named Hannah. The other was named Peninnah. Peninnah had children, but Hannah didn’t.

3Year after year Elkanah went up from his town to Shiloh. He went there to worship and sacrifice to the Lord who rules over all. Hophni and Phinehas served as priests of the Lord at Shiloh. They were the two sons of Eli. 4Every year at Shiloh, the day would come for Elkanah to offer a sacrifice. On that day, he would give a share of the meat to his wife Peninnah. He would also give a share to each of her sons and daughters. 5But he would give two shares of meat to Hannah. That’s because he loved her. He also gave her two shares because the Lord had kept her from having children. 6Peninnah teased Hannah to make her angry. She did it because the Lord had kept Hannah from having children. 7Peninnah teased Hannah year after year. Every time Hannah would go up to the house of the Lord, Elkanah’s other wife would tease her. She would keep doing it until Hannah cried and wouldn’t eat. 8Her husband Elkanah would say to her, “Hannah, why are you crying? Why don’t you eat? Why are you so unhappy? Don’t I mean more to you than ten sons?”

9One time when they had finished eating and drinking in Shiloh, Hannah stood up. Eli the priest was sitting on his chair by the doorpost of the Lord’s house. 10Hannah was very sad. She wept and wept. She prayed to the Lord. 11She made a promise to him. She said, “Lord, you rule over all. Please see how I’m suffering! Show concern for me! Don’t forget about me! Please give me a son! If you do, I’ll give him back to the Lord. Then he will serve the Lord all the days of his life. He’ll never use a razor on his head. He’ll never cut his hair.”

12As Hannah kept on praying to the Lord, Eli watched her lips. 13She was praying in her heart. Her lips were moving. But she wasn’t making a sound. Eli thought Hannah was drunk. 14He said to her, “How long are you going to stay drunk? Stop drinking your wine.”

15“That’s not true, sir,” Hannah replied. “I’m a woman who is deeply troubled. I haven’t been drinking wine or beer. I was telling the Lord all my troubles. 16Don’t think of me as an evil woman. I’ve been praying here because I’m very sad. My pain is so great.”

17Eli answered, “Go in peace. May the God of Israel give you what you have asked him for.”

18She said, “May you be pleased with me.” Then she left and had something to eat. Her face wasn’t sad anymore.

19Early the next morning Elkanah and his family got up. They worshiped the Lord. Then they went back to their home in Ramah. Elkanah slept with his wife Hannah. And the Lord blessed her. 20So after some time, Hannah became pregnant. She had a baby boy. She said, “I asked the Lord for him.” So she named him Samuel.

Hannah Gives Samuel to the Lord

21Elkanah went up to Shiloh to offer the yearly sacrifice to the Lord. He also went there to keep a promise he had made. His whole family went with him. 22But Hannah didn’t go. She said to her husband, “When the boy doesn’t need me to breast-feed him anymore, I’ll take him to the Lord’s house. I’ll give him to the Lord there. He’ll stay there for the rest of his life.”

23Her husband Elkanah told her, “Do what you think is best. Stay here at home until Samuel doesn’t need you to breast-feed him anymore. May the Lord make his promise to you come true.” So Hannah stayed home. She breast-fed her son until he didn’t need her milk anymore.

24When the boy didn’t need her to breast-feed him anymore, she took him with her to Shiloh. She took him there even though he was still very young. She brought him to the Lord’s house. She brought along a bull that was three years old. She brought 36 pounds of flour. She also brought a bottle of wine. The bottle was made out of animal skin. 25After the bull was sacrificed, Elkanah and Hannah brought the boy to Eli. 26Hannah said to Eli, “Pardon me, sir. I’m the woman who stood here beside you praying to the Lord. And that’s just as sure as you are alive. 27I prayed for this child. The Lord has given me what I asked him for. 28So now I’m giving him to the Lord. As long as he lives he’ll be given to the Lord.” And there Eli worshiped the Lord.