ዘፍጥረት 43 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 43:1-34

የዮሴፍ ወንድሞች ዳግመኛ ወደ ግብፅ መሄዳቸው

1ራቡ አሁንም በምድሪቱ ላይ እንደ ጸና ነበር፤ 2ከግብፅ ያመጡትንም እህል በልተው ከጨረሱ በኋላ፣ አባታቸው “እስቲ እንደ ገና ወርዳችሁ፣ ጥቂት እህል ሸምቱልን” አላቸው።

3ይሁዳ ግን እንዲህ አለው፤ “ያ ሰውየው ‘ወንድማችሁን ይዛችሁ ካልመጣችሁ ዳግመኛ ፊቴን አታዩም’ ብሎ በጥብቅ አስጠንቅቆናል፤ 4ወንድማችን ከእኛ ጋር እንዲወርድ ከፈቀድህ ወደዚያ ሄደን እህል እንሸምትልሃለን፤ 5እርሱን የማትልከው ከሆነ ግን እኛም ወደዚያ አንወርድም፤ ያም ሰው፣ ‘ወንድማችሁን ይዛችሁ ካልመጣችሁ ዳግመኛ ፊቴን አታዩም’ ብሎናል።”

6እስራኤልም፣ “ሌላ ወንድም አለን ብላችሁ ለዚያ ሰው በመንገር ለምን ይህን ችግር እንዲደርስብኝ አደረጋችሁ?” ሲል ጠየቃቸው።

7እነርሱም፣ “ሰውየው ስለ ራሳችንና ስለ ቤተ ሰባችን አጥብቆ ጠየቀን፤ እንደ ገናም ‘አባታችሁ አሁንም በሕይወት አለ? ሌላስ ወንድም አላችሁ?’ ሲል ጠየቀን። እኛም ለጥያቄው መልስ ሰጠነው። ታዲያ፣ ‘ወንድማችሁን ይዛችሁ ወደዚህ እንድትመጡ’ እንደሚል እንዴት ማወቅ እንችል ነበር?” ብለው መለሱለት።

8ይሁዳም አባቱን እስራኤልን እንዲህ አለው “ልጁን ከእኔ ጋር ስደደው፤ እኛም በቶሎ እንሂድ፤ ይህ ከሆነ፣ አንተም፣ እኛም፣ ልጆቻችንም አንሞትም፤ እንተርፋለን። 9ስለ ልጁ ደኅንነት እኔ ራሴ ኀላፊ ነኝ፤ ስለ እርሱም በግል ተጠያቂ እሆናለሁ፤ እርሱንም በደኅና መልሼ ባላመጣውና እዚህ በፊትህ ባላቆመው ለዘላለም በደለኛው እኔ ልሁን። 10ይህን ያህል ባንዘገይ ኖሮ፣ እስካሁን ሁለት ጊዜ ደርሰን መመለስ በቻልን ነበር።”

11ከዚህ በኋላ አባታቸው እስራኤል እንዲህ አላቸው፤ “ነገሩ እንዲህ ከሆነስ ይህን አድርጉ፤ ምድሪቱ ከምታፈራው ምርጥ ነገሮች ጥቂት በለሳን፣ ጥቂት ማር፣ ሽቱ፣ ከርቤ፣ ተምርና ለውዝ በየስልቻችሁ ይዛችሁ ለዚያ ሰው እጅ መንሻ ውሰዱለት። 12በየስልቾቻችሁ አፍ ላይ የተገኘውን ብር መመለስ ስላለባችሁ፣ ዕጥፍ ገንዘብ ያዙ፤ ያ በየስልቾቻችሁ ውስጥ የተገኘው ብር ምናልባት በስሕተት የመጣ ሊሆን ይችላል። 13ወንድማችሁንም ይዛችሁ ወደ ሰውየው በቶሎ ሂዱ። 14ሌላውን ወንድማችሁንና ብንያምን ይዛችሁ ለመመለስ እንድትችሉ ሁሉን የሚችል43፥14 ዕብራይስጡ ኤልሻዳይ ይላል። አምላክ በምሕረቱ የዚያን ሰው ልብ ያራራላችሁ። እንግዲህ ልጆቼንም ባጣ ምን አደርጋለሁ፤ ያመጣውን እቀበላለሁ።”

15ሰዎቹም እጅ መንሻውን፣ የብሩን ዕጥፍ እንዲሁም ብንያምን ይዘው ተነሡ፤ ወደ ግብፅም በፍጥነት ወረዱ፤ ዮሴፍም ፊት ቀረቡ። 16ዮሴፍ ብንያምን ከወንድሞቹ ጋር ባየው ጊዜ የቤቱን አዛዥ፣ “እነዚህን ሰዎች ወደ ቤት ይዘሃቸው ሂድ፤ ዛሬ ቀትር ላይ አብረውኝ ስለሚበሉ ፍሪዳ ተጥሎ ምሳ ይዘጋጅ” አለው።

17አዛዡም ዮሴፍ የነገረውን አደረገ፤ ሰዎቹንም ወደ ዮሴፍ ቤት ወሰዳቸው። 18ሰዎቹም ወደ ዮሴፍ ቤት በመወሰዳቸው ፈሩ፤ እነርሱም፣ “ወደዚህ የመጣነው፣ ቀደም ሲል እዚህ መጥተን ስንመለስ በየስልቾቻችን ውስጥ ተመልሶ በተጨመረው ብር ሰበብ ነው። ሰውየው ጥቃት ሊፈጽምብን፣ አስገድዶ ባሮቹ ሊያደርገንና አህዮቻችንን ሊቀማን ይፈልጋል” ብለው ሠጉ።

19ወደ ዮሴፍ ቤት አዛዥ ቀርበው፣ በቤቱ መግቢያ ላይ አነጋገሩት፤ 20“እንዲህም አሉት፤ ጌታችን ሆይ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ እህል ለመሸመት ወደዚህ መጥተን ነበር፤ 21ነገር ግን ለዐዳር በሰፈርንበት ቦታ የየስልቾቻችንን አፍ ስንከፍት፣ እያንዳንዳችን በስልቾቻችን አፍ ላይ፣ ብራችንን ሙሉውን አገኘነው። ገንዘቡንም ይኸው መልሰን ይዘን መጥተናል። 22አሁንም እህል መሸመቻ የሚሆነን ተጨማሪ ብር ይዘን መጥተናል፤ ያኔ ገንዘቡን በየስልቾቻችን ውስጥ ማን መልሶ እንዳስቀመጠው ግን አናውቅም” አሉት።

23የቤቱ አዛዥም፣ “አይዟችሁ አትፍሩ፤ በየስልቾቻችሁ ውስጥ ያገኛችሁትን ገንዘብ የሰጣችሁ የእናንተም የአባቶቻችሁም አምላክ (ኤሎሂም) ነው፤ እኔ እንደ ሆንሁ ብሩን ተቀብያለሁ” አላቸው። ከዚያም ስምዖንን አውጥቶ አገናኛቸው።

24የቤቱ አዛዥ ሰዎቹን ወደ ዮሴፍ ቤት አስገብቶ እግራቸውን የሚታጠቡበት ውሃ አቀረበላቸው፤ ለአህዮቻቸውም የሚበሉት ገፈራ ሰጣቸው። 25ምሳ በዚያ እንደሚበሉ ተነግሯቸው ስለ ነበር፣ ዮሴፍ በቀትር ከመግባቱ በፊት እጅ መንሻዎቻቸውን ለማበርከት ተዘጋጁ።

26ዮሴፍም ወደ ቤቱ ሲገባ ያመጧቸውን እጅ መንሻዎች አበረከቱለት፤ ወደ መሬት ዝቅ ብለውም እጅ ነሡት። 27ዮሴፍም ስለ ደኅንነታቸው ጠየቃቸው፤ ከዚያም “ሽማግሌ አባት እንዳላችሁ ነግራችሁኝ ነበር፤ ደኅና ነው? አሁንም በሕይወት አለ?” አላቸው።

28እነርሱም መልሰው፣ “አገልጋይህ አባታችን አሁንም በሕይወት አለ፤ ደኅና ነው” በማለት ወደ መሬት ዝቅ ብለው በአክብሮት እጅ ነሡት።

29ዮሴፍ በዐይኑ ሲቃኝ የእናቱን ልጅ ብንያምን አየና፣ “ያ የነገራችሁኝ ታናሽ ወንድማችሁ ይህ ነው?” ብሎ ጠየቃቸው። ብንያምንም፣ “ልጄ፤ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ይባርክህ” አለው። 30ዮሴፍ ወንድሙን በማየቱ ስሜቱ በጥልቅ ስለ ተነካ፣ ፈጥኖ ከፊታቸው ገለል አለ፤ ሰወር ያለ ቦታም ፈልጎ፣ ዕልፍኙ ውስጥ አለቀሰ።

31ፊቱን ከታጠበ በኋላ ተመልሶ፣ ስሜቱን በመቈጣጠር፣ “ማእድ ይቅረብ” አለ።

32ለዮሴፍ ለብቻው ቀረበለት፤ ለወንድሞቹም ለብቻቸው ቀረበላቸው፤ እንዲሁም ከእርሱ ጋር ለሚበሉት ግብፃውያን ደግሞ ሌላ ገበታ ቀረበላቸው፤ ምክንያቱም ግብፃውያን ከዕብራውያን ጋር አብሮ መመገብን እንደ ጸያፍ ይቈጥሩት ነበር። 33ወንድማማቾቹ ከበኵሩ እስከ ታናሹ እንደየዕድሜያቸው በዮሴፍ ፊት በተርታ ተቀምጠው ነበር፤ በመገረምም እርስ በርሳቸው ተያዩ። 34ከዮሴፍ ገበታ ላይ እየተነሣ ለእያንዳንዳቸው ምግብ ሲቀርብ፣ የብንያም ድርሻ ከሌሎቹ አምስት ዕጥፍ ነበር። እነርሱም እንዲህ ባለ ሁኔታ አብረውት ተደሰቱ፤ እስኪረኩም ጠጡ።

Thai New Contemporary Bible

ปฐมกาล 43:1-34

การเดินทางไปอียิปต์ครั้งที่สอง

1ขณะนั้นการกันดารอาหารยังคงรุนแรงอยู่ 2เมื่อข้าวที่พวกเขาเอามาจากอียิปต์หมดแล้ว บิดาก็พูดกับพวกเขาว่า “จงกลับไปซื้ออาหารมาให้เราอีกหน่อย”

3แต่ยูดาห์พูดกับบิดาว่า “คนๆ นั้นกำชับไว้ว่า ‘เจ้าจะไม่ได้รับอนุญาตให้มาพบเรา ถ้าไม่พาน้องชายคนเล็กมาด้วย’ 4ถ้าพ่อยอมให้น้องไปกับพวกเรา พวกเราก็จะลงไปอียิปต์เพื่อซื้ออาหารมาให้พ่อ 5แต่ถ้าพ่อไม่ยอมให้น้องไป พวกเราก็จะไม่ไป เพราะเจ้านายคนนั้นสั่งไว้ว่า ‘เจ้าจะไม่ได้รับอนุญาตให้มาพบเรา ถ้าไม่พาน้องชายคนเล็กมาด้วย’ ”

6อิสราเอลผู้เป็นบิดาจึงถามว่า “ทำไมเจ้านำปัญหามาให้เราเช่นนี้ เจ้าไปบอกเขาทำไมว่ามีน้องชายอีกคนหนึ่ง?”

7พวกเขาตอบว่า “ก็เขาเจาะจงถามถึงพวกเราและครอบครัวของเรา เขาถามเราว่า ‘พ่อของเจ้ายังมีชีวิตอยู่หรือ? เจ้ามีน้องอีกคนหนึ่งไหม?’ เราเพียงแต่ตอบไปตามที่เขาถาม เราจะไปรู้หรือว่าเขาจะสั่งว่า ‘จงพาน้องชายของพวกเจ้าลงมาที่นี่’?”

8แล้วยูดาห์ก็พูดกับอิสราเอลบิดาของเขาว่า “ให้น้องไปกับเราเถิด เราจะได้ออกเดินทางทันที เพื่อว่าพวกเรา ตัวพ่อ และลูกๆ ของเราจะไม่ต้องอดตาย 9ตัวข้าเองจะรับประกันความปลอดภัยของเขา ให้พ่อถือว่าข้าเป็นผู้รับผิดชอบเขาเอง ถ้าข้าพาเขากลับมาให้พ่อเห็นหน้าไม่ได้ ก็ขอให้เป็นตราบาปติดตัวข้าไปตลอดชีวิต 10ถ้าพวกเราไม่มัวรีรออยู่เช่นนี้ ป่านนี้พวกเราคงไปและกลับมาเป็นครั้งที่สองแล้ว”

11ในที่สุดอิสราเอลก็พูดกับพวกเขาว่า “หากต้องเป็นเช่นนี้ ก็ให้ทำดังนี้ก็แล้วกัน คือพวกเจ้าจงเอาของดีที่สุดในดินแดนของเรา ได้แก่ยางไม้ น้ำผึ้ง เครื่องเทศ มดยอบ ถั่วพิสทาชิโอ และอัลมอนด์ใส่กระสอบไปเป็นของกำนัลแด่ชายผู้นั้น 12เอาเงินไปสองเท่าด้วย จะได้คืนเงินที่ติดมาในกระสอบ นี่อาจจะเป็นเรื่องผิดพลาดก็ได้ 13จงพาน้องไปด้วย ไปพบชายผู้นั้นทันที 14ขอพระเจ้าผู้ทรงฤทธิ์ทรงเมตตาพวกเจ้าเมื่ออยู่ต่อหน้าชายผู้นั้น เขาจะได้ปล่อยสิเมโอนและเบนยามินกลับมาพร้อมกับพวกเจ้า ส่วนเราถ้าจะต้องไว้ทุกข์ก็ต้องยอม”

15พวกเขาจึงนำของกำนัลและเงินสองเท่าพร้อมกับเบนยามิน รีบเดินทางลงไปอียิปต์และเข้าพบโยเซฟ 16เมื่อโยเซฟเห็นเบนยามินมาด้วยจึงสั่งคนต้นเรือนว่า “จงพาชายเหล่านี้ไปที่บ้านของข้า แล้วฆ่าสัตว์สักตัวหนึ่งเตรียมอาหารไว้ พวกเขาจะกินอาหารกลางวันกับข้า”

17เขาก็ทำตามคำสั่ง แล้วพาชายเหล่านั้นไปยังบ้านของโยเซฟ 18พวกเขาตกใจกลัวมากเมื่อถูกพามาที่บ้านของโยเซฟ พวกเขาต่างคิดว่า “พวกเราถูกพามาที่นี่เพราะเงินที่ถูกใส่คืนให้เราในกระสอบเมื่อคราวก่อนแน่ๆ เลย เขาต้องการจะใส่ความเรา เล่นงานเรา แล้วก็จับตัวพวกเราเป็นทาสพร้อมทั้งริบลาของพวกเรา”

19ดังนั้นพวกเขาจึงไปหาคนต้นเรือนของโยเซฟที่ประตูบ้านและพูดว่า 20“ขอโทษขอรับท่าน คราวก่อนเมื่อพวกเราเดินทางมาซื้ออาหารที่นี่ 21คืนแรกที่พวกเราแวะพักแรม พวกเราได้เปิดกระสอบออกมาดูก็เห็นเงินค่าข้าวอยู่ที่ปากกระสอบของพวกเราแต่ละคนตามจำนวนที่พวกเราจ่ายไปพอดี ดังนั้นพวกเราจึงเอามาคืน 22พวกเราได้นำเงินมาเพิ่มอีกเพื่อที่จะซื้ออาหาร พวกเราไม่รู้ว่าใครนำเงินเหล่านี้ใส่เข้าไปในกระสอบของพวกเรา”

23คนต้นเรือนตอบว่า “ทำใจให้สงบเถิด อย่ากลัวเลย พระเจ้าของพวกท่าน พระเจ้าของบิดาท่านทรงประทานทรัพย์สินที่อยู่ในกระสอบให้ท่าน เราได้รับเงินจากพวกท่านเรียบร้อยแล้ว” แล้วคนต้นเรือนก็พาสิเมโอนออกมาพบพวกเขา

24จากนั้นคนต้นเรือนพาพวกเขาเข้าไปในบ้านของโยเซฟ เอาน้ำมาให้ล้างเท้า และให้อาหารแก่ลาของพวกเขา 25พวกเขาก็เตรียมของกำนัลเพื่อมอบให้แก่โยเซฟซึ่งจะมาถึงตอนเที่ยง เพราะพวกเขาได้ยินว่าจะรับประทานอาหารด้วยกันที่นั่น

26เมื่อโยเซฟมาถึงบ้าน พวกพี่น้องก็มอบของกำนัลให้เขา และหมอบกราบเขาลงถึงดิน 27โยเซฟถามถึงทุกข์สุขของพวกเขาและถามอีกว่า “พ่อผู้ชราที่พวกเจ้าพูดถึงยังสุขสบายดีไหม? ยังมีชีวิตอยู่หรือเปล่า?”

28พวกเขาตอบว่า “พ่อของเราผู้รับใช้ของท่าน ยังมีชีวิตอยู่และสบายดี” และพวกเขาก็หมอบกราบราบกับพื้นต่อหน้าโยเซฟ

29ขณะที่โยเซฟมองดูพวกเขาและเห็นเบนยามินน้องชายร่วมมารดา จึงถามว่า “คนนี้หรือคือน้องชายคนสุดท้องที่พวกเจ้าพูดถึง?” แล้วพูดกับเบนยามินว่า “ลูกเอ๋ย ขอพระเจ้าทรงเมตตาเจ้าเถิด” 30เมื่อโยเซฟได้พบหน้าน้องชายก็ตื้นตันใจเหลือล้นจนต้องผลุนผลันออกไปหาที่ร้องไห้ เขาจึงเข้าไปร้องไห้ในห้องส่วนตัว

31จากนั้นเขาก็ล้างหน้าล้างตา ควบคุมอารมณ์ และกลับออกมาสั่งว่า “ยกอาหารมาเถิด”

32พวกเขาจัดอาหารให้โยเซฟรับประทานแต่ลำพัง โต๊ะของพี่น้องแยกต่างหาก ส่วนชาวอียิปต์ที่ร่วมรับประทานอาหารกับโยเซฟก็อยู่อีกโต๊ะหนึ่ง คนอียิปต์ไม่นั่งร่วมโต๊ะกับคนฮีบรูเพราะถือว่าเป็นสิ่งน่ารังเกียจสำหรับชาวอียิปต์ 33โยเซฟจัดให้ชายเหล่านั้นแต่ละคนนั่งเรียงกันตามลำดับอายุ ตั้งแต่คนโตสุดถึงคนเล็กสุด ทำให้ชายเหล่านั้นมองหน้ากันด้วยความสงสัย 34เมื่ออาหารส่วนของพวกเขาถูกส่งมาจากโต๊ะของโยเซฟ เบนยามินได้มากเป็นห้าเท่าของคนอื่นๆ พวกเขาก็กินดื่มร่วมกับโยเซฟจนอิ่มหนำสำราญ