ዘፀአት 28 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 28:1-43

ልብሰ ተክህኖ

1“ካህናት ሆነው ያገለግሉኝ ዘንድ ከእስራኤላውያን መካከል ወንድምህ አሮንን ከወንዶች ልጆቹ ከናዳብ፣ ከአብዩድ፣ ከአልዓዛርና ከኢታምር ጋር ወደ አንተ አቅርባቸው። 2ለእርሱም ማዕረግና ክብር ለመስጠት ለወንድምህ ለአሮን የተቀደሱ መጐናጸፊያዎችን አብጅለት። 3ካህን ሆኖ እንዲያገለግለኝ የተለየ ይሆን ዘንድ ጥበብ ለሰጠኋቸው በዚህ ጕዳይ ላይ ጥበበኛ ለሆኑ ሰዎች ሁሉ ለአሮን መጐናጸፊያዎችን እንዲሠሩለት ንገራቸው። 4የሚሠሯቸው መጐናጸፊያዎች የደረት ልብስ ኤፉድ ቀሚስ፣ ጥልፍ ሸሚዝ፣ ጥምጥምና መታጠቂያ ናቸው፤ ካህን ሆነው ያገለግሉኝ ዘንድ የተቀደሱ መጐናጸፊያዎችን ለአሮንና ለወንድ ልጆቹ ይሠራሉ። 5ወርቅ፣ ሰማያዊ፣ ሐምራዊ፣ ቀይ ማግና እንዲሁም ቀጭን በፍታ ይጠቀሙ።

ኤፉድ

28፥6-14 ተጓ ምብ – ዘፀ 39፥2-7

6“የጥልፍ ዐዋቂዎች ኤፉዱን ከወርቅ፣ ከሰማያዊ፣ ከሐምራዊ፣ ከቀይ ማግና በቀጭኑ ከተፈተለ በፍታ ይሥሩት። 7መተሳሰር እንዲችል ሆኖ፣ ዳርና ዳር ከሚገኙት ከሁለቱ ጐኖች ጋር የተያያዙ ሁለት የትከሻ ንጣዮች ይኑሩት። 8በጥበብ የተጠለፈው የወገብ መታጠቂያ ከወርቅ፣ ከሰማያዊ፣ ከሐምራዊ፣ ከቀይ ማግና በቀጭኑ ከተፈተለ ሐር ከኤፉድ ጋር አንድ ወጥ ሆኖ የተሠራ ይሁን።

9“ሁለት የመረግድ ድንጋዮች ውሰድና የእስራኤልን ልጆች ስሞቻቸውን ቅረጽባቸው። 10እንደ ልደታቸው ቅደም ተከተል ስድስቱን ስሞች በአንዱ ድንጋይ ላይ የቀሩትንም ስሞች በሌላው ላይ ቅረጽባቸው። 11የቅርጽ ሠራተኛ ማኅተም እንደሚቀርጽ የእስራኤልን ልጆች ስም በሁለቱ ድንጋዮች ላይ ቅረጽ፤ ከዚያም ድንጋዮቹን በወርቅ ፈርጥ ክፈፋቸው፤ 12ለእስራኤል ልጆች መታሰቢያ ድንጋዮች ይሆኑ ዘንድ በኤፉዱ ትከሻ ላይ ካሉት ንጣዮች ጋር አያይዛቸው፤ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት መታሰቢያ እንዲሆኑ አሮን ስሞቹን በትከሻው ላይ ይሸከማቸው። 13የወርቅ ፈርጦችን አብጅ፤ 14እንደ ገመድ ያሉ ሁለት በንጹሕ ወርቅ የተጐነጐኑ ድሪዎችን አብጅተህ ከፈርጡ ጋር አያይዛቸው።

የደረት ኪስ

28፥15-28 ተጓ ምብ – ዘፀ 39፥8-21

15“የፍርድ መስጫውን የደረት ኪስ ብልኅ ሠራተኛ እንደሚሠራው አድርገህ አብጀው፤ ልክ እንደ ኤፉዱ ከወርቅ፣ ከሐምራዊ፣ ከቀይ ማግና በቀጭኑ ከተፈተለ በፍታ አብጀው። 16ርዝመቱ አንድ ስንዝር፣ ስፋቱ አንድ ስንዝር28፥16 ወደ 22 ሴንቲ ሜትር ያህል ነው። ሆኖ ባለ አራት ማእዘንና በድርቡ የታጠፈ ይሁን። 17ከዚያም በላዩ ላይ በአራት ረድፍ የከበሩ ድንጋዮች አድርግበት፤ በመጀመሪያው ረድፍ ሰርዲዮን፣ ቶጳዝዮን፣ የሚያበረቀርቅ ዕንቍ፤ 18በሁለተኛውም ረድፍ በሉር፣ ሰንፔር28፥18 ወይም፣ ላፒስ ላዙሊ፣ አልማዝ፤ 19በሦስተኛው ረድፍ ያክንት፣ ኬልቄዶን፣ አሜቴስጢኖስ፤ 20በአራተኛውም ረድፍ ቢረሌ፣ መረግድና ኢያስጲድ28፥20 የእነዚህ የከበሩ ማዕድኖች ትክክለኛ ማንነት በትክክል አይታወቅም። አድርግበት፤ በወርቅ ፈርጥም ክፈፋቸው። 21የዐሥራ ሁለቱ ነገዶች ስሞች እንደ ማኅተም የተቀረጸባቸው ለእያንዳንዱ የእስራኤል ልጆች ስም ዐሥራ ሁለት ድንጋዮች ይሁኑ።

22“ለደረት ኪሱ ከንጹሕ ወርቅ እንደ ገመድ ሆኖ የተጌጠ ጕንጕን አብጅለት። 23ለእርሱም ሁለት የወርቅ ቀለበቶች አብጅተህ ከደረት ኪሱ ሁለት ጐኖች ጋር አያይዘው። 24ሁለቱን የወርቅ ጕንጕኖች በደረት ኪሱ ጐኖች ላይ ካሉት ቀለበቶች ጋር አያይዛቸው። 25ሌሎቹን የጕንጕን ጫፎች በፊት ላይ ካለው ኤፉድ በትከሻው ላይ ካሉት ንጣዮች ጋር በማጋጠም ከሁለቱ የወርቅ ፈርጦች ጋር አያይዛቸው። 26ሁለት የወርቅ ቀለበቶች አበጅተህ ከኤፉዱ ቀጥሎ ባለው በውስጠኛ ጠርዝ ላይ፣ በሌላ በኩል ካሉት ሁለት የደረት ኪስ ጐኖች ጋር አያይዛቸው። 27ሁለት ተጨማሪ የወርቅ ቀለበቶች አበጅተህ ከኤፉዱ መታጠቂያ ከፍ ብሎ ከመጋጠሚያው አጠገብ ካለው በኤፉዱ ፊት ለፊት፣ በትከሻ ላይ ካሉት ንጣዮች ግርጌ ጋር አያይዘው። 28የደረት ኪሱም ቀለበቶች፣ የደረት ኪሱ ከኤፉዱ ጋር እንዳይላቀቅ፣ ከመታጠቂያው ጋር በማገናኘት በሰማያዊ ገመድ ከኤፉዱ ቀለበቶች ጋር ይያያዙ።

29“አሮን ወደ መቅደሱ በሚገባበት ጊዜ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ለዘላለም መታሰቢያ ይሆን ዘንድ የእስራኤልን ልጆች ስሞች በፍርድ መስጫው ደረት ኪስ በልቡ ላይ ይሸከም። 30ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት በሚገባበት ጊዜ በአሮን ልብ ላይ ይሆኑ ዘንድ ኡሪሙንና ቱሚሙን በደረት ኪሱ አድርግ፤ ስለዚህ አሮን ሁልጊዜ ለእስራኤላውያን የፍርድ መስጫውን በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት በልቡ ላይ ይሸከማል።

ሌሎቹ አልባሳት

28፥31-43 ተጓ ምብ – ዘፀ 39፥22-31

31“የኤፉዱ ቀሚስ ሙሉ በሙሉ ከሰማያዊ ጨርቅ ይሁን፤ 32ከላይ በኩል በመካከሉ ዐንገትጌ አድርገህ አብጀው፤ እንዳይቀደድም በማስገቢያው ዙሪያ እንደ ክሳድ ያለ ዝምዝም ጠርዝ28፥32 በዕብራይስጡ የዚህ ቃል ትክክለኛ ፍችው አይታወቅም። ሥራለት። 33በጨርቁ ጠርዝ ዙሪያ ከሰማያዊ፣ ከሐምራዊና ከቀይ ማግ ሮማኖቹን፣ በመካከሉም የወርቅ ሻኵራዎችን አብጅ። 34የወርቅ ሻኵራዎቹና ሮማኖቹ በጨርቁ ጠርዝ ዙሪያ በመፈራረቅ ይሆናሉ። 35አሮንም በአገልግሎቱ ጊዜ ይህን መልበስ አለበት፤ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወደ መቅደሱ በገባና ከመቅደሱ ሲወጣ እንዳይሞት የሻኵራዎቹ ድምፅ ይሰማል።

36“ከንጹሕ ወርቅ ዝርግ ሳሕን አበጅተህ፣ ‘ቅዱስ እግዚአብሔር (ያህዌ)’ በማለት በማኅተም ላይ እንደሚቀረጽ ቅረጸው። 37ከመጠምጠሚያው ጋር እንዲያያዝ ሰማያዊ ፈትል እሰርበት፤ እርሱም በመጠምጠሚያው ፊት በኩል ይሁን። 38ይህም በአሮን ግንባር ላይ ይሆናል፤ እስራኤላውያን ለይተው በሚያቀርቧቸው በማናቸውም የተቀደሱ ስጦታዎች ውስጥ ያለውን በደል ይሸከማል፤ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ተቀባይነት እንዲኖራቸው ሁልጊዜ በአሮን ግንባር ላይ ይሆናል።

39“ሸሚዙን ከቀጭን በፍታ ሥራ፤ መጠምጠሚያውንም ከቀጭን በፍታ አብጀው፤ መታጠቂያውንም ጥልፍ ጠላፊ የሠራው ይሁን። 40የአሮን ወንድ ልጆች ክብርና ማዕረግ እንዲኖራቸው ሸሚዞችን፣ መታጠቂያዎችን፣ የራስ ማሰሪያዎችን አብጅላቸው። 41እነዚህን ልብሶች ለአሮንና ለወንድ ልጆቹ ካለበስህ በኋላ ቅባቸው፤ ካናቸው፤ ካህናት ሆነው ያገለግሉኝም ዘንድ ቀድሳቸው።

42“ከወገብ ጀምሮ እስከ ጭን የሚደርስ ሰውነትን የሚሸፍን ከበፍታ የተሠራ የውስጥ ቍምጣ አብጅ። 43አሮንና ወንድ ልጆቹ ወደ መገናኛው ድንኳን በሚገቡበት ጊዜ ወይም በመቅደሱ ለማገልገል ወደ መሠዊያው ሲቀርቡ፣ በደል ፈጽመው እንዳይሞቱ እነዚህን መልበስ አለባቸው።

“ለአሮንና ለትውልዶቹ ይህ የዘላለም ሥርዐት ይሆናል።

Thai New Contemporary Bible

อพยพ 28:1-43

เครื่องแต่งกายปุโรหิต

1“จงสถาปนาอาโรนพี่ชายของเจ้าและบรรดาบุตรชายของเขาคือ นาดับ อาบีฮู เอเลอาซาร์ และอิธามาร์ ให้ทำหน้าที่ปุโรหิตรับใช้เรา 2จงทำเครื่องแต่งกายบริสุทธิ์สำหรับอาโรนให้งดงามและสมเกียรติ 3จงกำชับช่างผู้ชำนาญทุกคนซึ่งเราให้สติปัญญาในเชิงช่างแก่เขา ให้ทำเครื่องแต่งกายสำหรับอาโรน สำหรับการชำระเขาให้บริสุทธิ์และแยกเขาไว้เพื่อเขาจะปฏิบัติหน้าที่ปุโรหิตรับใช้เรา 4เครื่องแต่งกายที่ให้ทำได้แก่ ทับทรวง เอโฟด เสื้อคลุม เสื้อตัวในที่ทอขึ้น ผ้าโพกศีรษะ และสายคาดเอว และจงทำเครื่องแต่งกายบริสุทธิ์พิเศษสำหรับอาโรนพี่ชายของเจ้าและบรรดาบุตรชายของเขาด้วย เพื่อเขาจะได้รับใช้เราในฐานะปุโรหิต 5โดยให้ช่างใช้ทองคำ ด้ายสีน้ำเงิน ม่วง และแดง และผ้าลินินเนื้อดี

เอโฟด

(อพย.39:2-7)

6“จงให้ช่างฝีมือผู้ชำนาญทำเอโฟดโดยใช้ทองคำ ด้ายสีน้ำเงิน ม่วง และแดง และผ้าลินินเนื้อดี 7ประกอบด้วยชิ้นหน้าและชิ้นหลัง มีแถบสองชิ้นที่บ่าโยงมุมสำหรับผูกเข้าด้วยกัน 8ทำสายคาดเอวอย่างประณีตด้วยทองคำ ด้ายสีน้ำเงิน ม่วง และแดง และผ้าลินินเนื้อดีทอเข้าเป็นชิ้นเดียวกับเอโฟด

9“จงเอาโกเมนสองชิ้นจารึกชื่อบุตรชายทั้งหลายของอิสราเอล 10จารึกชิ้นละหกชื่อตามลำดับการกำเนิดของพวกเขา 11จงจารึกชื่อบุตรชายทั้งหลายของอิสราเอลลงบนโกเมนทั้งสองชิ้นนั้นด้วยวิธีเดียวกันกับที่ช่างเจียระไนสลักตรา แล้วฝังโกเมนสองชิ้นนั้นบนเรือนทอง 12จงร้อยโกเมนทั้งสองชิ้นนี้เข้ากับแถบบ่าเอโฟด เพื่อเป็นหินอนุสรณ์ถึงประชากรอิสราเอล อาโรนจะต้องแบกชื่อของพวกเขา เพื่อองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงระลึกถึงพวกเขาเสมอ 13จงทำเรือนทองสองเรือน 14และทำสร้อยเกลียวสองเส้นลักษณะคล้ายเชือกด้วยทองคำบริสุทธิ์และติดสร้อยนั้นเข้ากับเรือนทองทั้งสอง

ทับทรวง

(อพย.39:8-21)

15“แล้วจงให้ช่างฝีมือผู้ชำนาญทำทับทรวงสำหรับการตัดสินโดยใช้ทองคำ ด้ายสีน้ำเงิน ม่วง และแดง และผ้าลินินเนื้อดีเหมือนกับที่ใช้ทำเอโฟด 16ทับทรวงนี้จะเป็นผ้าสี่เหลี่ยมจัตุรัสขนาดหนึ่งคืบ28:16 คือ ประมาณ 22 เซนติเมตรพับสองทบ 17แล้วฝังอัญมณีสี่แถวเข้ากับทับทรวง แถวแรกได้แก่ ทับทิม บุษราคัม และนิล 18แถวที่สองได้แก่ พลอยขี้นกการเวก ไพฑูรย์ และมรกต 19แถวที่สามได้แก่ พลอยสีม่วง โมรา และเพทายม่วง 20แถวที่สี่ได้แก่ เพทาย โกเมน และมณีโชติ28:20 ในภาษาฮีบรูอัญมณีเหล่านี้บางชิ้นไม่สามารถระบุได้ชัดเจน ทั้งหมดนี้ฝังไว้บนเรือนทอง 21อัญมณีสิบสองเม็ดนี้ แต่ละเม็ดสลักชื่อบุตรชายแต่ละคนของอิสราเอลแทนทั้งสิบสองเผ่าเหมือนสลักตรา

22“จงทำสร้อยเกลียวทองคำบริสุทธิ์ลักษณะคล้ายเชือกสำหรับทับทรวง 23ทำห่วงทองคำสองห่วงคล้องสร้อยเกลียวเข้ากับมุมทั้งสองของทับทรวง 24ผูกสร้อยเกลียวทองคำทั้งสองเส้นเข้ากับห่วงที่มุมทับทรวง 25ส่วนปลายอีกด้านของสร้อยเกลียวติดเข้ากับเรือนทองทั้งสอง แล้วติดเข้ากับแถบบ่าทั้งสองของเอโฟดตรงด้านหน้า 26ทำห่วงทองคำสองห่วงติดกับอีกสองมุมของทับทรวงตรงขอบด้านในชิดกับเอโฟด 27ทำห่วงทองคำอีกสองห่วงติดที่ปลายล่างของแถบบ่าตรงด้านหน้าของเอโฟด ชิดกับตะเข็บเหนือสายคาดเอวของเอโฟด 28ห่วงของทับทรวงจะผูกเข้ากับห่วงของเอโฟดโดยใช้ด้ายถักสีน้ำเงินติดเข้ากับสายคาดเอว เพื่อไม่ให้ทับทรวงเลื่อนหลุดจากเอโฟด

29“เมื่อใดก็ตามที่อาโรนเข้าไปในวิสุทธิสถาน เขาจะแบกชื่อบุตรทั้งหลายของอิสราเอลแนบหัวใจของเขาบนทับทรวงแห่งการตัดสิน แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงระลึกถึงพวกเขาอยู่เสมอ 30จงสอดอูริมและทูมมิมไว้ในช่องระหว่างทบของทับทรวงด้วย เพื่อสองสิ่งนี้จะได้แนบใจของอาโรนเวลาเข้าเฝ้าองค์พระผู้เป็นเจ้าดังนั้นอาโรนจะมีเครื่องมือในการตัดสินสำหรับชนอิสราเอลแนบใจเสมอต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า

เครื่องแต่งกายปุโรหิตชิ้นอื่นๆ

(อพย.39:22-31)

31“จงทำเสื้อคลุมเข้าชุดกับเอโฟดด้วยผ้าสีน้ำเงินทั้งตัว 32มีช่องตรงกลางสำหรับสวมเข้าทางศีรษะและมีแถบทอรอบคอเสื้อ28:32 ในภาษาฮีบรูคำนี้มีความหมายไม่ชัดเจนเพื่อไม่ให้เสื้อขาด 33จงทำผลทับทิมด้วยด้ายสีน้ำเงิน ม่วง และแดงไว้รอบชายเสื้อคลุม ติดลูกพรวนทองคำสลับกับผลทับทิม 34ลูกพรวนทองคำจะต้องสลับกับผลทับทิมรอบชายเสื้อคลุม 35อาโรนต้องสวมเสื้อนี้ทุกครั้งที่เข้าไปปฏิบัติหน้าที่ คนจะได้ยินเสียงลูกพรวนขณะที่เขาเข้าออกต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าในวิสุทธิสถาน เพื่อเขาจะไม่ตาย

36“จงทำแผ่นทองคำบริสุทธิ์และสลักว่า ‘บริสุทธิ์แด่องค์พระผู้เป็นเจ้า’ 37จงร้อยแผ่นทองนี้เข้ากับด้านหน้าของผ้าโพกศีรษะของอาโรนโดยใช้ด้ายถักสีน้ำเงิน 38เพื่ออาโรนจะได้คาดแผ่นทองนี้บนหน้าผาก และแบกมลทินความผิดซึ่งเกี่ยวเนื่องกับเครื่องบูชาศักดิ์สิทธิ์ที่ประชากรอิสราเอลนำมาถวาย เขาจะต้องคาดไว้เสมอเพื่อองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงยอมรับประชากร

39“จงทอเสื้อตัวในจากผ้าลินินเนื้อดีและใช้ผ้าอย่างเดียวกันนี้ทำผ้าโพกศีรษะด้วย และจงทำสายคาดเอวปักด้วยฝีมือประณีต 40จงทำเสื้อตัวใน สายคาดเอว และแถบคาดหน้าผากสำหรับบุตรชายทั้งหลายของอาโรนให้สง่างามและสมเกียรติ 41จงให้อาโรนพี่ชายของเจ้ากับบรรดาบุตรชายของเขาสวมเครื่องแต่งกายเหล่านี้ แล้วเจิมและสถาปนาพวกเขา ชำระพวกเขาให้บริสุทธิ์ และแยกพวกเขาไว้เพื่อพวกเขาจะได้รับใช้เราในฐานะปุโรหิต

42“จงทำเครื่องแต่งกายชั้นในด้วยผ้าลินินเพื่อสวมปกปิดร่างกายตั้งแต่เอวถึงต้นขา 43อาโรนและบรรดาบุตรชายของเขาจะต้องสวมเครื่องแต่งกายเหล่านี้ทุกครั้งที่เข้าไปในเต็นท์นัดพบหรือเข้าใกล้แท่นบูชาเพื่อปรนนิบัติในวิสุทธิสถาน พวกเขาจะได้ไม่มีความผิดและต้องโทษถึงชีวิต

“นี่จะต้องเป็นข้อปฏิบัติถาวรสำหรับอาโรนและวงศ์วานของเขาสืบไป