ዘዳግም 13 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 13:1-18

ሌሎች አማልክትን ማምለክ

1ነቢይ ወይም ሕልም ዐላሚ ከመካከልህ ተነሥቶ ምልክት ወይም ድንቅ አደርጋለሁ ቢልህ፣ 2የተናገረው ምልክት ወይም ድንቅ ቢፈጸም፣ “አንተ የማታውቃቸውን ሌሎች አማልክት እናምልካቸው” ቢልህ፣ 3አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በፍጹም ልባችሁና በፍጹም ነፍሳችሁ ትወድዱት እንደ ሆነ ያውቅ ዘንድ ሊፈትናችሁ ነውና፣ የዚያን ነቢይ ቃል ወይም ሕልም ዐላሚውን አትስማ። 4አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ተከተሉት፤ ፍሩት፤ ትእዛዞቹንም ጠብቁ፤ ታዘዙት፤ አገልግሉት፤ ከእርሱም ጋር ተጣበቁ። 5ከግብፅ ባወጣችሁና ከባርነት ምድር በዋጃችሁ በአምላካችሁ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ላይ እንድታምፁ ተናግሯልና፣ አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትከተሉት ካዘዛችሁ መንገድ እንድትመለሱ አድርጓልና፣ ያ ነቢይ ወይም ሕልም ዐላሚ ይገደል፤ ስለዚህ ክፉውን ከመካከልህ አስወግድ።

6የእናትህ ልጅ ወንድምህ፣ ወንድ ወይም ሴት ልጅህ፣ ወይም የምትወድዳት ሚስትህ ወይም የልብ ጓደኛህ፣ (አንተም ሆንህ አባቶችህ የማታውቋቸውን አማልክት) “ሄደን ሌሎችን አማልክት እናምልክ” ብሎ በስውር ሊያስትህ ቢሞክር፣ 7በቅርብም ሆነ በሩቅ፣ ከአንዱ የምድር ጫፍ እስከ ሌላው ድረስ በዙሪያህ ያሉትን የአሕዛብ አማልክት እናምልክ ቢልህ፣ 8እሺ አትበለው፤ ወይም አታዳምጠው፤ አትራራለት፤ አትማረው፤ ወይም አትሸሽገው። 9ያለማመንታት ግደለው፤ እርሱንም ለመግደል በመጀመሪያ የአንተ እጅ፣ ከዚያም በኋላ የሕዝቡ ሁሉ እጅ ይነሣ። 10የባርነት ምድር ከሆነው ከግብፅ ካወጣህ ከአምላክህ ከእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ሊያርቅህ ፈልጓልና እስኪሞት ድረስ በድንጋይ ውገረው። 11ከዚያም እስራኤል ሁሉ ሰምተው ይፈራሉ፤ ከመካከልህም ማንም እንደዚህ ያለውን ክፉ ነገር ዳግም አያደርግም።

12አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትኖርባቸው ከሚሰጥህ ከተሞች በአንዲቱ ውስጥ እንዲህ ሲባል ብትሰማ፣ 13ክፉ ሰዎች ከመካከላችሁ ተነሥተው አንተ የማታውቃቸውን፣ “ሌሎች አማልክትን ሄደን እናምልክ” በማለት የከተማቸውን ሕዝብ እያሳቱ ቢሆን፣ 14ጕዳዩን አጣራ፤ መርምር፤ በሚገባም ተከታተል፤ ነገሩ እውነት ሆኖ ከተገኘና ይህ አስጸያፊ ነገር በመካከልህ መፈጸሙ ከተረጋገጠ፣ 15በዚያች ከተማ የሚኖሩትን ሁሉ በሰይፍ ግደላቸው፤ ከተማዪቱን ከነሕዝቧና ከነቀንድ ከብቷ ፈጽሞ ደምስሳት13፥15 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ነገር ወይም አንድን ሰው ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን የሚያሳይ ነው።16በከተማዪቱ የተገኘውን የምርኮ ዕቃ ሁሉ በአደባባይዋ መካከል ላይ ሰብስበህ፣ ከተማዪቱን ከነምርኮዋ እንዳለ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሚቀርብ መሥዋዕት አድርገህ በሙሉ አቃጥል። ለዘላለም እንደ ፈረሰች ትቅር፤ ተመልሳም አትሠራ። 17እግዚአብሔር (ያህዌ) ከብርቱ ቍጣው ይመለስ ዘንድ ዕርም ነገሮች በእጅህ አይገኙ13፥17 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ነገር ወይም አንድን ሰው ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን የሚያሳይ ነው።፤ እርሱ ምሕረቱን ያሳይሃል፤ ይራራልሃል፤ ለአባቶችህ በመሐላ ተስፋ በሰጠው መሠረት ቍጥርህን ያበዛዋል፤ 18ይህም የሚሆነው ዛሬ እኔ የምሰጥህን ትእዛዞቹን ሁሉ በመጠበቅና መልካም የሆነውን በአምላክህ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት በማድረግ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ስለ ታዘዝህለት ነው።

Thai New Contemporary Bible

เฉลยธรรมบัญญัติ 13:1-18

อย่านมัสการพระอื่น

1หากมีผู้เผยพระวจนะหรือผู้ที่ทำนายอนาคตโดยอ้างความฝันอยู่ในหมู่พวกท่าน และประกาศกับพวกท่านว่าจะเกิดหมายสำคัญหรือปาฏิหาริย์ 2และหากหมายสำคัญหรือปาฏิหาริย์ที่เขาบอกไว้เป็นจริงขึ้นมา และเขากล่าวว่า “ให้เราไปติดตามพระอื่นๆ เถิด” (บรรดาพระที่ท่านไม่รู้จัก) “ให้เราไปกราบไหว้พระเหล่านั้นเถิด” 3อย่าไปฟังคำของผู้เผยพระวจนะหรือผู้ฝันเห็นเหตุการณ์คนนั้นเลย พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงทดสอบดูว่าท่านรักพระองค์ด้วยสุดจิตสุดใจหรือไม่ 4พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านคือผู้ที่ท่านต้องติดตามและยำเกรง จงปฏิบัติตามพระบัญชาและเชื่อฟังพระองค์ จงปรนนิบัติและยึดมั่นในพระองค์ 5ผู้เผยพระวจนะและผู้ฝันเห็นเหตุการณ์นั้นจะต้องถูกประหาร เพราะเขาสั่งสอนให้กบฏต่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านผู้ได้ทรงนำท่านออกจากอียิปต์และทรงไถ่ท่านจากแดนทาส ผู้นั้นพยายามชักจูงท่านให้หันเหจากทางที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงสั่งให้ท่านเดินตาม ท่านต้องขจัดความชั่วออกไปจากหมู่พวกท่าน

6หากพี่น้องของท่านเอง หรือบุตรชายบุตรสาว หรือภรรยาที่รัก หรือเพื่อนสนิท แอบชักจูงท่านโดยกล่าวว่า “ให้เราไปนมัสการพระอื่นๆ เถิด” (พระซึ่งท่านหรือบรรพบุรุษไม่เคยรู้จักมาก่อน 7พระของชนชาติต่างๆ รอบตัวท่าน ไม่ว่าใกล้หรือไกลจากสุดปลายแผ่นดินข้างหนึ่งไปอีกข้างหนึ่ง) 8อย่าคล้อยตามหรือรับฟัง อย่าสงสารเขา ไม่ต้องไว้ชีวิตหรือปกป้องเขาเลย 9จงประหารเขา ตัวท่านเองจงลงมือประหารเขาเป็นคนแรก แล้วให้ประชาชนทั้งปวงลงมือด้วย 10จงเอาหินขว้างเขาให้ตาย เพราะเขาพยายามชักจูงท่านให้หันเหจากพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านผู้ทรงนำท่านออกจากอียิปต์ จากแดนทาส 11แล้วอิสราเอลทั้งปวงจะได้ยินเรื่องราวและจะได้เข็ดขยาด และไม่มีใครในพวกท่านทำสิ่งชั่วร้ายแบบนั้นอีก

12หากท่านได้ยินคนกล่าวถึงเมืองใดที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านประทานให้ท่านเป็นที่พักอาศัย 13ว่ามีกลุ่มคนชั่วชักจูงชาวเมืองให้หลงผิดไปโดยกล่าวว่า “ให้เราไปนมัสการพระอื่นๆ เถิด” (พระซึ่งท่านไม่รู้จักมาก่อน) 14ท่านต้องสืบสวนไล่เลียงไต่ถามอย่างถี่ถ้วน หากเป็นความจริงและพิสูจน์ได้ว่ามีการกระทำอันน่ารังเกียจเช่นนั้นในหมู่ท่าน 15ท่านจงประหารชาวเมืองทั้งหมดด้วยดาบ ทำลายล้าง13:15 คำนี้ในภาษาฮีบรูหมายถึงสิ่งของหรือบุคคลที่ถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าแล้วไม่อาจเรียกคืนได้ มักจะต้องทำลายให้หมดสิ้นไป เช่นเดียวกับข้อ 17ทั้งประชาชนและฝูงสัตว์ให้สิ้นซาก 16แล้วนำข้าวของทั้งหมดที่ยึดได้มากองไว้กลางลานเมืองและจุดไฟเผาทั้งเมืองและข้าวของให้สิ้น เป็นเครื่องเผาบูชาแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน เมืองนั้นจะกลายเป็นซากปรักหักพังตลอดไป อย่าสร้างขึ้นใหม่อีกเลย 17อย่าให้พบสิ่งที่ต้องทำลายทิ้งในมือของท่านเลย แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงหันจากพระพิโรธอันรุนแรงมาเมตตาและรักเอ็นดูท่าน และให้ท่านทวีจำนวนขึ้นตามที่ทรงสัญญาไว้กับบรรพบุรุษของท่าน 18เพราะท่านเชื่อฟังพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน ปฏิบัติตามพระบัญชาทั้งปวงซึ่งข้าพเจ้าแจ้งท่านในวันนี้ และทำสิ่งที่ถูกต้องในสายพระเนตรของพระองค์