ዘሌዋውያን 8 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 8:1-36

አሮንና ልጆቹ ካህናት ሆነው መሾማቸው

8፥1-36 ተጓ ምብ – ዘፀ 29፥1-37

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“አሮንንና ልጆቹን፣ ልብሰ ተክህኖውን፣ የመቅቢያ ዘይቱን፣ ለኀጢአት መሥዋዕት የሚሆነውን ወይፈን፣ ሁለቱን አውራ በጎችና እርሾ ሳይገባበት የተጋገረው ቂጣ ያለበትን መሶብ አምጣ፤ 3ማኅበሩን በሙሉ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ሰብስብ።” 4ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው አደረገ፤ ማኅበሩም በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ተሰበሰበ።

5ሙሴም ማኅበሩን፣ “እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲደረግ ያዘዘው ይህ ነው” አላቸው። 6ሙሴም አሮንንና ልጆቹን ወደ ፊት አወጣቸው፤ በውሃም ዕጠባቸው። 7አሮንን እጀ ጠባብ አለበሰው፤ መቀነት አስታጠቀው፤ ቀሚስ አጠለቀለት፤ ኤፉድ ደረበለት፤ በልዩ ጥበብ በተጠለፈው መታጠቂያ ኤፉዱን አስታጠቀው፤ በላዩም አሰረው፤ 8የደረት ኪሱን በላዩ አደረገለት፤ በደረት ኪሱም ውስጥ ኡሪምንና ቱሚምን አኖረ። 9እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘውም መሠረት፣ ሙሴ ጥምጥሙን በአሮን ራስ ላይ አደረገ፤ በጥምጥሙም ላይ በፊት ለፊቱ በኩል የተቀደሰውን የወርቅ አክሊል አደረገለት።

10ሙሴም መቅቢያ ዘይቱን ወሰደ፤ ማደሪያ ድንኳኑንና በውስጡ የሚገኘውን ሁሉ ቀብቶ ቀደሰ። 11ከዘይቱም ጥቂት ወስዶ በመሠዊያው ላይ ሰባት ጊዜ ረጨ፤ ይቀድሳቸውም ዘንድ መሠዊያውን ከነመገልገያ ዕቃው ሁሉ እንዲሁም የመታጠቢያ ሳሕኑን ከነማስቀመጫው በዘይት ቀባ። 12ከመቅቢያ ዘይቱም በአሮን ራስ ላይ አፈሰሰ፤ የተቀደሰ እንዲሆንም ቀባው። 13እግዚአብሔርም (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት ሙሴ፣ የአሮንን ልጆች ወደ ፊት አቅርቦ እጀ ጠባብ አለበሳቸው፤ መታጠቂያ አስታጠቃቸው፤ ቆብም ደፋላቸው።

14ሙሴም የኀጢአት መሥዋዕት የሆነውን ወይፈን አመጣ፤ አሮንና ልጆቹም በወይፈኑ ራስ ላይ እጃቸውን ጫኑ። 15ሙሴም ወይፈኑን ዐረደ፤ ደሙንም ወስዶ መሠዊያውን ያነጻ ዘንድ በጣቱ የመሠዊያውን ቀንዶች ሁሉ ቀባ፤ የቀረውንም ደም በመሠዊያው ሥር አፈሰሰው። ለመሠዊያውም እንዲህ አድርጎ ያስተሰርይለት ዘንድ ቀደሰው። 16ሙሴም የሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሁሉ፣ የጕበቱን ሽፋን፣ ኵላሊቶችንና ሥባቸውን ወስዶ በመሠዊያው ላይ አቃጠለ። 17ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት ወይፈኑን፣ ቈዳውን፣ ሥጋውንና ፈርሱን ከሰፈር ውጭ አቃጠለ።

18ሙሴ ለሚቃጠል መሥዋዕት የሚሆነውን አውራ በግ አቀረበ፤ አሮንና ልጆቹም እጃቸውን በበጉ ላይ ጫኑ። 19ሙሴም በጉን ዐርዶ ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ረጨ። 20በጉንም በየብልቱ ቈራረጠ፤ ጭንቅላቱን፣ ብልቶቹንና ሥቡን አቃጠለ። 21ሆድ ዕቃውንና እግሮቹን በውሃ አጠበ፤ ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት፣ በጉን በሙሉ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ፣ ሽታውም ደስ የሚያሰኝ የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጎ በመሠዊያው ላይ አቃጠለው።

22ሙሴ ለቅድስና የሚሆነውን ሌላ አውራ በግ አቀረበ፤ አሮንና ልጆቹም እጆቻቸውን በበጉ ራስ ላይ ጫኑ። 23ሙሴ አውራ በጉን ዐረደ፤ ከደሙም ጥቂት ወስዶ የአሮንን ቀኝ ጆሮ ጫፍ፣ የቀኝ እጁን አውራ ጣትና የቀኝ እግሩን አውራ ጣት አስነካ፤ 24የአሮንንም ልጆች ወደ ፊት ጠራ፤ ከደሙም ጥቂት ወስዶ የቀኝ ጆሯቸውን ጫፍ፣ የቀኝ እጃቸውን አውራ ጣትና የቀኝ እግራቸውን አውራ ጣት አስነካ፤ የቀረውንም ደም በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ረጨ። 25ሥቡን፣ ላቱን፣ ሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሥብ ሁሉ፣ የጕበቱን ሽፋን፣ ሁለቱን ኵላሊቶችና ሥባቸውን እንዲሁም ቀኝ ወርቹን ወሰደ፤ 26በእግዚአብሔርም (ያህዌ) ፊት ካለው፣ ያለ እርሾ የተጋገረ ዳቦ ካለበት መሶብ ላይ አንድ ኅብስት፣ አንድ በዘይት የተጋገረ ዳቦ እንዲሁም ስስ ቂጣ ወስዶ በሥቦቹና በቀኝ ወርቹ ላይ አኖረ። 27እነዚህንም ሁሉ ለአሮንና ለልጆቹ በእጃቸው ሰጣቸው፤ እነርሱም የሚወዘወዝ መሥዋዕት አድርገው በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወዘወዙት። 28ሙሴም ከእጃቸው ተቀብሎ፣ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ፣ ሽታውም ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት አድርጎ በመሠዊያው ላይ በሚቃጠለው መሥዋዕት ላይ አቃጠለው። 29ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት፣ ድርሻው የሆነውን ክህነት የመስጫውን አውራ በግ ፍርምባ ወስዶ የሚወዘወዝ መሥዋዕት በማድረግ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወዘወዘው።

30ቀጥሎም ሙሴ በመቅቢያው ዘይትና በመሠዊያው ላይ ካለው ደም ጥቂት ወስዶ፣ በአሮንና በልብሱ እንዲሁም በአሮን ልጆችና በልብሳቸው ላይ ረጨ፤ በዚህም ሁኔታ አሮንንና ልብሱን፣ ልጆቹንና ልብሳቸውን ቀደሰ።

31ሙሴም አሮንና ልጆቹን እንዲህ አላቸው፤ “ሥጋውን በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ቀቅሉት፤ በዚያም፣ ‘አሮንና ልጆቹ ይብሉት’ ተብዬ በታዘዝሁት8፥31 ወይም ብዬ ባዘዝሁት መሠረት፣ በክህነት መስጫው መሥዋዕት መሶብ ውስጥ ካለው ኅብስት ጋር ብሉት፤ 32የተረፈውንም ሥጋና ኅብስት በእሳት አቃጥሉ። 33የክህነት መቀበያችሁ ሥርዐት እስከሚፈጸምበት እስከ ሰባት ቀን ድረስ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ቈዩ፤ ሥርዐቱንም ለመፈጸም ሰባት ቀን ይወስዳልና። 34ዛሬ የተፈጸመው ይህ ሥርዐት ለእናንተ ማስተስረያ እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘው ነው። 35እንዳትሞቱ ሰባቱን ቀንና ሌሊት ከመገናኛው ድንኳን ደጃፍ አትለዩ፤ የእግዚአብሔርንም (ያህዌ) ሥርዐት ጠብቁ፤ የታዘዝሁት እንዲህ ነውና።” 36አሮንና ልጆቹም እግዚአብሔር (ያህዌ) በሙሴ አማካይነት ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

利未記 8:1-36

膏立亞倫父子們做祭司

1耶和華對摩西說: 2「你把亞倫父子們帶來,也要帶聖衣、膏油、一頭作贖罪祭的公牛、兩隻公綿羊和一籃無酵餅, 3然後把全體會眾招聚到會幕門前。」 4摩西按照耶和華的指示行事,會眾都聚集在會幕門前。

5摩西告訴會眾:「這是耶和華吩咐我做的事。」 6他把亞倫父子們帶來,用水洗他們。 7摩西亞倫穿上內袍,束上腰帶,穿上外袍,套上以弗得,用精巧的帶子把以弗得繫在亞倫身上, 8然後給他戴上胸牌,把烏陵和土明放在胸牌內, 9再把禮冠戴在他頭上,在禮冠前繫上金牌,即聖冠,都遵照耶和華的吩咐。

10摩西拿膏油抹聖幕和聖幕裡的一切物件,使它們聖潔; 11再用膏油在祭壇上灑七次,又抹祭壇和祭壇上的器具、洗濯盆和盆座,使它們聖潔。 12然後,摩西把膏油倒在亞倫頭上膏立他,使他聖潔。 13摩西又把亞倫的兒子們帶來,給他們穿上內袍,束上腰帶,裹上頭巾,都遵照耶和華的吩咐。

14摩西牽來那頭作贖罪祭的公牛,亞倫父子們把手放在牛頭上。 15摩西宰了牛,用手指蘸一些牛血抹在祭壇的四角上,以潔淨祭壇;把剩下的血倒在祭壇腳旁,使祭壇聖潔。 16他取出遮蓋內臟的脂肪、肝葉、兩個腎臟和腎臟上的脂肪,放在壇上焚燒, 17又照耶和華的吩咐,把公牛的皮、肉和糞便帶到營外燒掉。

18然後,摩西獻上作燔祭的公綿羊,亞倫父子們把手放在羊頭上。 19摩西宰了那隻羊,將羊血灑在祭壇周圍; 20把羊切成塊,焚燒羊頭、肉塊和脂肪; 21用水洗淨羊的內臟和腿,放在壇上焚燒,作蒙耶和華悅納的馨香火祭,都遵照耶和華的吩咐。

22摩西獻上另一隻為授聖職而獻的公綿羊。亞倫父子們把手放在羊頭上。 23摩西宰了羊,將一些羊血抹在亞倫的右耳垂、右手大拇指和右腳大腳趾上。 24他又把亞倫的兒子們帶來,將一些血抹在他們的右耳垂、右手大拇指和右腳大腳趾上,然後把剩下的血都灑在祭壇四周。 25他取下羊的右腿和脂肪,即肥尾巴、遮蓋內臟的脂肪、肝葉、兩個腎臟和腎臟上的脂肪, 26又從放在耶和華面前盛無酵餅的籃子中取一個無酵餅、一個油餅和一個薄餅,放在羊的右腿和脂肪上。 27他把這些放在亞倫父子們的手上,作為搖祭在耶和華面前搖一搖。 28隨後,他從他們手上拿過這些祭物,放在祭壇的燔祭上焚燒,作為授聖職時獻的祭。這是蒙耶和華悅納的馨香火祭。 29摩西又把祭牲的胸肉作為搖祭在耶和華面前搖一搖,這是他授聖職時所應得之份,都遵照耶和華的吩咐。

30摩西拿了一些膏油和壇上的血,灑在亞倫和他的衣服上,也灑在他兒子們和他們的衣服上,使亞倫父子們和他們的衣服聖潔。

31摩西亞倫父子們說:「你們要照我的指示在會幕門口煮祭肉吃,也要吃籃子裡為授聖職而獻的餅。 32吃剩的肉和餅,你們要燒掉。 33你們的聖職禮為期七天,這七天之內,你們不可走出會幕門口。 34今天所做的這一切都是耶和華吩咐的,是為你們贖罪。 35七天之內,你們必須日夜待在會幕門口,要遵守耶和華的吩咐,免得你們死亡。這是耶和華對我的吩咐。」 36於是,亞倫父子們遵行了耶和華藉摩西吩咐的一切。