ዕዝራ 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዕዝራ 1:1-11

ቂሮስ ምርኮኞቹ እንዲመለሱ ፈቀደ

1፥1-3 ተጓ ምብ – 2ዜና 36፥22-23

1ቂሮስ የፋርስ ንጉሥ በሆነ በመጀመሪያው ዓመት፣ እግዚአብሔር የቂሮስን መንፈስ አነሣሥቶ በመንግሥቱ ሁሉ ዐዋጅ እንዲያስነግርና ይህም በጽሑፍ እንዲሰፍር አደረገ፤ ይህ የሆነው በኤርምያስ አፍ የተነገረው የእግዚአብሔር ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።

2“የፋርስ ንጉሥ ቂሮስ የሚለው ይህ ነው፤

“ ‘የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር የምድርን መንግሥታት ሁሉ ሰጥቶኛል፤ በይሁዳ ምድር በምትገኘው በኢየሩሳሌምም ለእርሱ ቤተ መቅደስ እንድሠራ አዝዞኛል። 3ከሕዝቡ መካከል በእናንተ ዘንድ የሚኖር ማናቸውም ሰው አምላኩ ከእርሱ ጋር ይሁን፤ በይሁዳ ወደምትገኘው ወደ ኢየሩሳሌም ይውጣና በዚያ ለሚኖረው አምላክ፣ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ይሥራ። 4ባሉበት ስፍራ የሚቀሩ በየትኛውም አገር የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ በኢየሩሳሌም ለሚገኘው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ስጦታ እንዲሆን በበጎ ፈቃድ ከሚያቀርቡት መባ በተጨማሪ ብርና ወርቅ፣ ዕቃና እንስሳ በመስጠት ይርዷቸው።’ ”

5ከዚያም እግዚአብሔር መንፈሳቸውን ያነሣሣው የይሁዳና የብንያም ቤተ ሰብ አለቆች እንዲሁም ካህናቱና ሌዋውያኑ ሁሉ ለመሄድና በኢየሩሳሌም የሚገኘውን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለመሥራት ተዘጋጁ። 6ጎረቤቶቻቸውም ሁሉ በበጎ ፈቃድ ከሰጡት መባ በተጨማሪ ከብርና ከወርቅ የተሠሩ ዕቃዎችን፣ ቍሳቍስን፣ እንስሶችንና ሌሎች ጠቃሚ የሆኑ ስጦታዎችንም በመለገስ ረዷቸው። 7ከዚህም በላይ ንጉሡ ቂሮስ፣ ናቡከደነፆር ከኢየሩሳሌም ወስዶ በአማልክቱ1፥7 ወይም፣ በአምላኩ ቤተ ጣዖት ያኖራቸውን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ንዋያተ ቅድሳት አወጣ። 8የፋርስ ንጉሥ ቂሮስ በግምጃ ቤቱ ኀላፊ በሚትሪዳጡ አማካይነት ንዋያተ ቅድሳቱ እንዲመጡና በይሁዳው ገዥ በሰሳብሳር ፊት እንዲቈጠሩ አደረገ።

9የዕቃው ዝርዝር ይህ ነበር፤

የወርቅ ሳሕን 30የብር ሳሕን 1,000ዝርግ የብር ሳሕን1፥9 በዕብራይስጡ የዚህ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም። 2910ጐድጓዳ የወርቅ ሳሕን 30ባለ ግጣም የብር ጐድጓዳ ሳሕን 410ሌሎች ቍሳቍስ 1,000

11በአጠቃላይ አምስት ሺሕ አራት መቶ የወርቅና የብር ዕቃዎች ነበሩ።

ሰሳብሳር ምርኮኞቹ ከባቢሎን ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሱ ይህን ሁሉ ዕቃ ይዞ ወጣ።

Thai New Contemporary Bible

เอสรา 1:1-11

ไซรัสช่วยเชลยกลับภูมิลำเนา

(2พศด.36:22-23)

1ในปีที่หนึ่งของรัชกาลกษัตริย์ไซรัสแห่งเปอร์เซีย องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำให้พระดำรัสของพระองค์ที่ตรัสผ่านทางเยเรมีย์สำเร็จ โดยองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงดลใจกษัตริย์ไซรัสแห่งเปอร์เซียให้ออกประกาศทั่วราชอาณาจักรของพระองค์ และให้บันทึกเป็นลายลักษณ์อักษรความว่า

2“กษัตริย์ไซรัสแห่งเปอร์เซียตรัสดังนี้ว่า

“ ‘พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์ได้ประทานราชอาณาจักรทั้งสิ้นของโลกนี้แก่ข้าพเจ้า และได้ทรงมอบหมายให้ข้าพเจ้าสร้างพระวิหารถวายแด่พระองค์ที่เยรูซาเล็มในเขตยูดาห์ 3ผู้ใดในหมู่พวกท่านที่เป็นประชากรของพระเจ้า ขอให้พระเจ้าของเขาสถิตกับเขา และให้เขากลับไปยังเยรูซาเล็มในยูดาห์และสร้างพระวิหารของพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอล พระเจ้าผู้ประทับในเยรูซาเล็ม 4ให้ประชาชนในถิ่นที่ผู้รอดชีวิตเหล่านี้อาศัยอยู่มอบเงิน ทอง ข้าวของ และฝูงสัตว์ พร้อมทั้งของถวายตามความสมัครใจเพื่อพระวิหารของพระเจ้าในเยรูซาเล็มแก่พวกเขา’ ”

5แล้วบรรดาหัวหน้าครอบครัวของเผ่ายูดาห์และเบนยามิน กับปุโรหิตและคนเลวี คือทุกคนที่พระเจ้าทรงดลใจ ก็เตรียมตัวขึ้นไปสร้างพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้าที่เยรูซาเล็ม 6เพื่อนบ้านทั้งปวงช่วยเหลือจุนเจือพวกเขาโดยให้เครื่องใช้ไม้สอยที่ทำจากเงินและทอง ข้าวของและฝูงสัตว์ พร้อมทั้งของมีค่าต่างๆ นอกเหนือจากของถวายตามความสมัครใจ 7นอกจากนี้กษัตริย์ไซรัสเองทรงมอบเครื่องใช้ไม้สอยต่างๆ ที่กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์ยึดไปจากพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้าในเยรูซาเล็มและได้เก็บไว้ในวิหารของเทพเจ้าของพระองค์1:7 หรือเทพเจ้าต่างๆ 8กษัตริย์ไซรัสแห่งเปอร์เซียทรงให้ขุนคลังมิทเรดาทนำเครื่องใช้เหล่านี้ออกมานับจำนวนแล้วมอบให้เชชบัสซาร์ซึ่งเป็นเจ้านายของยูดาห์

9รายการสิ่งของมีดังนี้ คือ

ชามทองคำ 30 ใบชามเงิน 1,000 ใบกระทะเงิน1:9 ในภาษาฮีบรูคำนี้มีความหมายไม่ชัดเจน29 ใบ10อ่างทองคำ 30 ใบอ่างเงินที่เข้าชุดกัน 410 ใบเครื่องใช้อื่นๆ 1,000 ชิ้น

11มีเครื่องใช้ทองและเงินทั้งสิ้น 5,400 ชิ้น เมื่อพวกเชลยออกจากบาบิโลนมายังเยรูซาเล็ม เชชบัสซาร์นำสิ่งของทั้งหมดนี้ไปด้วย