ዕብራውያን 13 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዕብራውያን 13:1-25

የመጨረሻ ምክር

1እርስ በርሳችሁ እንደ ወንድማማች ተዋደዱ። 2እንግዶችን መቀበል አትርሱ፤ አንዳንዶች ይህን ሲያደርጉ፣ ሳያውቁ መላእክትን አስተናግደዋልና። 3በእስር ላይ ያሉትን ከእነርሱ ጋር እንደ ታሰራችሁ ሆናችሁ አስቧቸው፤ እንዲሁም በሰው እጅ የሚንገላቱትን ራሳችሁ መከራ እንደምትቀበሉ አድርጋችሁ አስቧቸው።

4ጋብቻ በሁሉም ዘንድ ይከበር፤ መኝታውም ንጹሕ ይሁን፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር በአመንዝሮችና በሴሰኞች ሁሉ ላይ ይፈርዳል። 5ራሳችሁን ከፍቅረ ንዋይ ጠብቁ፤ ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ኑሩ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር፣

“ከቶ አልተውህም፤

በፍጹም አልጥልህም” ብሏል።

6ስለዚህ በሙሉ ልብ፣

“ጌታ ረዳቴ ነው፤ አልፈራም፤

ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል?” እንላለን።

7የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን መሪዎቻችሁን አስቡ፤ የኑሯቸውን ፍሬ ተመልከቱ፤ በእምነታቸውም ምሰሏቸው። 8ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንት፣ ዛሬም ለዘላለምም ያው ነው።

9በልዩ ልዩ ዐይነት እንግዳ ትምህርቶች አትወሰዱ፤ ልባችን የሚጸናው በጸጋ እንጂ የምግብ ሥርዐት በመጠበቅ አይደለም፤ ይህን ሥርዐት የሚጠብቁት እንኳ በዚህ አልተጠቀሙም። 10በድንኳኒቱም የሚያገለግሉ ከዚያ ሊበሉ መብት ያላገኙበት መሠዊያ አለን።

11ሊቀ ካህናቱ ስለ ኀጢአት ስርየት የሚሆነውን የእንስሳት ደም ይዞ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ይገባል፤ የእንስሳቱ ሥጋ ግን ከሰፈር ውጭ ይቃጠላል። 12እንዲሁም ኢየሱስ በራሱ ደም አማካይነት ሕዝቡን ሊቀድስ ከከተማው በር ውጭ መከራን ተቀበለ። 13ስለዚህ እኛም እርሱ የተሸከመውን ውርደት ተሸክመን ከሰፈር ውጭ ወደ እርሱ እንውጣ። 14ምክንያቱም በዚህ ቋሚ ከተማ የለንም፤ ነገር ግን ወደ ፊት የምትመጣዋን ከተማ እንጠብቃለን።

15ስለዚህ ዘወትር የምስጋናን መሥዋዕት ይኸውም ለስሙ የሚመስክሩ የከንፈሮችን ፍሬ በኢየሱስ አማካይነት ለእግዚአብሔር እናቅርብ። 16ደግሞም መልካም ማድረግንና ያላችሁንም ከሌሎች ጋር መካፈልን አትርሱ፤ እግዚአብሔር ደስ የሚሰኘው እንደዚህ ባለው መሥዋዕት ነውና።

17ለመሪዎቻችሁ ታዘዙ፤ ተገዙላቸውም፤ ምክንያቱም እነርሱ በብርቱ የሚያስጠይቃቸው ነገር ስላለባቸው፣ ስለ ነፍሳችሁ ጕዳይ ይተጋሉ። ስለዚህ ሥራቸውን በሐዘን ሳይሆን በደስታ ማከናወን እንዲችሉ ታዘዟቸው፤ አለዚያ አይበጃችሁም።

18ለእኛ ደግሞ ጸልዩልን። በሁሉም መንገድ በመልካም አኗኗር ለመኖር የሚናፍቅ ንጹሕ ኅሊና እንዳለን ርግጠኞች ነን። 19በተለይም ወደ እናንተ በፍጥነት ተመልሼ እንድመጣ ትጸልዩልኝ ዘንድ ዐደራ እላችኋለሁ።

20በዘላለም ኪዳን ደም የበጎች ታላቅ እረኛ የሆነውን ጌታችን ኢየሱስን ከሞት ያስነሣው የሰላም አምላክ፣ 21ፈቃዱን እንድታደርጉ በመልካም ነገር ሁሉ ያስታጥቃችሁ፤ ደስ የሚያሰኘውንም በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእኛ ያድርግ፤ ለእርሱ እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።

22ወንድሞች ሆይ፤ የጻፍሁላችሁ መልእክት ዐጭር እንደ መሆኑ፣ የምክር ቃሌን በትዕግሥት እንድትቀበሉ ዐደራ እላችኋለሁ።

23ወንድማችን ጢሞቴዎስ እንደ ተፈታ ታውቁ ዘንድ እፈልጋለሁ፤ ቶሎ ከመጣ፣ ከእርሱ ጋር ላያችሁ እመጣለሁ።

24ለመሪዎቻችሁ ሁሉና ለቅዱሳን ሁሉ ሰላምታ አቅርቡልኝ።

ከኢጣሊያ የሆኑትም ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።

25ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።

Thai New Contemporary Bible

ฮีบรู 13:1-25

คำแนะนำสุดท้าย

1จงรักกันฉันพี่น้องสืบต่อไป 2อย่าลืมที่จะต้อนรับแขกแปลกหน้า เพราะโดยการทำเช่นนั้นบางคนได้ต้อนรับทูตสวรรค์โดยไม่รู้ตัว 3จงระลึกถึงบรรดาผู้ถูกจองจำอยู่เสมือนว่าท่านถูกจองจำร่วมกันกับเขา และจงระลึกถึงคนทั้งหลายที่ถูกข่มเหงราวกับว่าท่านเองกำลังทนทุกข์อยู่

4จงให้การแต่งงานเป็นที่นับถือสำหรับคนทั้งปวงและรักษาเตียงสมรสให้บริสุทธิ์ เพราะพระเจ้าจะทรงพิพากษาโทษคนล่วงประเวณีและคนทั้งปวงที่ผิดศีลธรรมทางเพศ 5จงรักษาชีวิตของท่านให้เป็นอิสระจากการรักเงินทองและจงพอใจในสิ่งที่ตนมี เพราะพระเจ้าได้ตรัสว่า

“เราจะไม่มีวันทอดทิ้งท่าน

เราจะไม่มีวันละทิ้งท่าน”13:5 ฉธบ.31:6

6ดังนั้นเราจึงกล่าวได้อย่างมั่นใจว่า

“องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเป็นผู้ช่วยเหลือข้าพเจ้า ข้าพเจ้าจะไม่กลัว

มนุษย์จะทำอะไรข้าพเจ้าได้เล่า?”13:6 สดด.118:6,7

7จงระลึกถึงบรรดาผู้นำของท่าน ผู้ได้กล่าวพระวจนะของพระเจ้าแก่ท่าน จงพิจารณาดูผลลัพธ์ของวิถีชีวิตของพวกเขาเหล่านั้นแล้วตามอย่างความเชื่อของพวกเขา 8พระเยซูคริสต์ทรงเป็นเหมือนเดิมเสมอ ทั้งเมื่อวานนี้ วันนี้ และสืบไปนิรันดร์

9อย่าหลงไปตามสารพันคำสอนแปลกๆ เป็นการดีที่จะให้ใจเราเข้มแข็งขึ้นด้วยพระคุณ ไม่ใช่ด้วยอาหารตามระเบียบพิธีซึ่งไม่ได้ให้คุณค่าใดๆ แก่ผู้รับประทาน 10เรามีแท่นบูชาซึ่งผู้ปฏิบัติหน้าที่ในพลับพลาไม่มีสิทธิ์รับประทานอาหารจากแท่นนั้น

11มหาปุโรหิตนำเลือดของสัตว์ต่างๆ เข้าไปในอภิสุทธิสถานเป็นเครื่องบูชาไถ่บาป แต่ร่างของสัตว์เหล่านั้นถูกนำไปเผานอกค่ายพัก 12พระเยซูก็เช่นกัน พระองค์ทรงทนทุกข์นอกประตูเมืองเพื่อชำระเหล่าประชากรให้บริสุทธิ์ด้วยพระโลหิตของพระองค์เอง 13ฉะนั้นให้เราทั้งหลายออกไปหาพระองค์ที่นอกค่าย ทนรับความอัปยศที่พระองค์ทรงแบกรับ 14เพราะที่นี่เราไม่มีนครอันถาวร แต่เรากำลังมองหานครซึ่งจะมาถึง

15เพราะฉะนั้นให้เราถวายการสรรเสริญเป็นเครื่องบูชาแด่พระเจ้าโดยทางพระเยซูตลอดไป คือถวายผลแห่งริมฝีปากที่กล่าวยอมรับพระนามของพระองค์ 16อย่าลืมที่จะทำความดีและแบ่งปันร่วมกับผู้อื่นเพราะพระเจ้าพอพระทัยเครื่องบูชาเช่นนี้

17ท่านทั้งหลายจงเชื่อฟังและยอมอยู่ใต้บังคับบัญชาผู้นำของท่านซึ่งเฝ้าดูแลท่านในฐานะเป็นผู้ที่ต้องรายงาน จงเชื่อฟังเขาเพื่อเขาจะทำหน้าที่ด้วยความชื่นใจ ไม่ใช่จำใจรับภาระซึ่งไม่เป็นประโยชน์อันใดแก่ท่าน

18จงอธิษฐานเผื่อเรา เราแน่ใจว่าเรามีจิตสำนึกที่บริสุทธิ์และปรารถนาจะดำเนินชีวิตอย่างน่านับถือในทุกด้าน 19ข้าพเจ้าขอร้องท่านเป็นพิเศษให้อธิษฐานขอให้ข้าพเจ้าได้กลับมาหาท่านในไม่ช้านี้

20ขอพระเจ้าแห่งสันติสุขผู้ซึ่งโดยโลหิตแห่งพันธสัญญานิรันดร์ได้ทรงให้พระเยซูเจ้าของเราผู้เป็นองค์พระผู้เลี้ยงผู้ยิ่งใหญ่แห่งฝูงแกะของพระเจ้าเป็นขึ้นจากตายนั้น 21ทรงให้ท่านทั้งหลายพรั่งพร้อมด้วยทุกสิ่งที่ดีเพื่อจะทำตามพระประสงค์ของพระองค์ และขอทรงกระทำการในเราทั้งหลายตามที่ชอบพระทัยพระองค์โดยทางพระเยซูคริสต์ ขอพระเกียรติสิริมีแด่พระองค์เสมอไปเป็นนิตย์ อาเมน

22พี่น้องทั้งหลาย ข้าพเจ้าขอให้ท่านอดทนรับฟังคำเตือนสติของข้าพเจ้าเพราะข้าพเจ้าเขียนจดหมายเพียงสั้นๆ มาถึงท่าน

23ข้าพเจ้าขอเรียนให้ท่านทราบว่าทิโมธีน้องของพวกเราได้รับการปล่อยตัวแล้ว หากเขามาถึงเร็วๆ นี้ข้าพเจ้าจะมาหาท่านทั้งหลายพร้อมกับเขา

24ข้าพเจ้าขอฝากความคิดถึงมายังบรรดาผู้นำของท่านตลอดจนประชากรทั้งปวงของพระเจ้า พวกพี่น้องจากอิตาลีฝากความคิดถึงมายังท่านทั้งหลาย

25ขอพระคุณดำรงอยู่กับท่านทั้งปวง