ዕብራውያን 1 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ዕብራውያን 1:1-14

ልጁ ከመላእክት በላይ ነው

1እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በተለያየ ጊዜና በልዩ ልዩ መንገድ በነቢያት በኩል ለአባቶቻችን ተናግሮ፣ 2በዚህ መጨረሻ ዘመን ግን ሁሉን ወራሽ ባደረገውና ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ ለእኛ ተናገረን። 3እርሱ የእግዚአብሔር ክብር ነጸብራቅና የባሕርዩ ትክክለኛ ምሳሌ ሆኖ፣ በኀያል ቃሉ ሁሉን ደግፎ ይዟል። የኀጢአት መንጻት ካስገኘ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ። 4ስለዚህ የወረሰው ስም ከመላእክት ስም እንደሚበልጥ ሁሉ፣ እርሱም ከመላእክት እጅግ የላቀ ሆኗል።

5እግዚአብሔር፣

“አንተ ልጄ ነህ፤

እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ፤”1፥5 ወይም እኔ ዛሬ አባት ሆንሁህ

ወይስ ደግሞ፣

“እኔ አባት እሆነዋለሁ፤

እርሱም ልጅ ይሆነኛል”

ያለው ከመላእክት ከቶ ለማን ነው? 6ደግሞም እግዚአብሔር በኵሩን ወደ ዓለም ሲያስገባ፣

“የእግዚአብሔር መላእክት ሁሉ1፥6 የሙት ባሕር ጥቅልሎችንና ሰብዓ ሊቃናትን ይመ ይስገዱለት” ይላል።

7ስለ መላእክትም ሲናገር፣

“መላእክቱን ነፋሳት፣

አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል ያደርጋል” ይላል።

8ስለ ልጁ ግን እንዲህ ይላል፤

“አምላክ ሆይ፤ ዙፋንህ ከዘላለም እስከ ዘላለም ጸንቶ ይኖራል፤

ጽድቅም የመንግሥትህ በትር ይሆናል፤

9ጽድቅን ወደድህ፤ ዐመፃን ጠላህ፤

ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ ከባልንጀሮችህ በላይ አስቀመጠህ፣

የደስታንም ዘይት ቀባህ።”

10ደግሞም እንዲህ ይላል፤

“ጌታ ሆይ፤ አንተ

በመጀመሪያ የምድርን መሠረት አኖርህ፤

ሰማያትም የእጆችህ ሥራ ናቸው።

11እነርሱ ይጠፋሉ፤ አንተ ግን ጸንተህ ትኖራለህ፤

ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃሉ፤

12እንደ መጐናጸፊያ ትጠቀልላቸዋለህ፤

እንደ ልብስም ይለወጣሉ።

አንተ ግን ያው አንተ ነህ፤

ዘመንህም ፍጻሜ የለውም።”

13እግዚአብሔር፣

“ጠላቶችህን የእግርህ መርገጫ እስከማደርግልህ ድረስ፣

በቀኜ ተቀመጥ”

ያለው ከመላእክት ከቶ ለማን ነው? 14መላእክት ሁሉ መዳንን የሚወርሱትን ለማገልገል የሚላኩ አገልጋይ መናፍስት አይደሉምን?

New International Version – UK

Hebrews 1:1-14

God’s final word: his Son

1In the past God spoke to our ancestors through the prophets at many times and in various ways, 2but in these last days he has spoken to us by his Son, whom he appointed heir of all things, and through whom also he made the universe. 3The Son is the radiance of God’s glory and the exact representation of his being, sustaining all things by his powerful word. After he had provided purification for sins, he sat down at the right hand of the Majesty in heaven. 4So he became as much superior to the angels as the name he has inherited is superior to theirs.

The Son superior to angels

5For to which of the angels did God ever say,

‘You are my Son;

today I have become your Father’1:5 Psalm 2:7?

Or again,

‘I will be his Father,

and he will be my Son’1:5 2 Samuel 7:14; 1 Chron. 17:13?

6And again, when God brings his firstborn into the world, he says,

‘Let all God’s angels worship him.’1:6 Deut. 32:43 (see Dead Sea Scrolls and Septuagint)

7In speaking of the angels he says,

‘He makes his angels spirits,

and his servants flames of fire.’1:7 Psalm 104:4

8But about the Son he says,

‘Your throne, O God, will last for ever and ever;

a sceptre of justice will be the sceptre of your kingdom.

9You have loved righteousness and hated wickedness;

therefore God, your God, has set you above your companions

by anointing you with the oil of joy.’1:9 Psalm 45:6,7

10He also says,

‘In the beginning, Lord, you laid the foundations of the earth,

and the heavens are the work of your hands.

11They will perish, but you remain;

they will all wear out like a garment.

12You will roll them up like a robe;

like a garment they will be changed.

But you remain the same,

and your years will never end.’1:12 Psalm 102:25-27

13To which of the angels did God ever say,

‘Sit at my right hand

until I make your enemies

a footstool for your feet’1:13 Psalm 110:1?

14Are not all angels ministering spirits sent to serve those who will inherit salvation?