ኤርምያስ 49 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 49:1-39

ስለ አሞን የተነገረ መልእክት

1ስለ አሞናውያን፤

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እስራኤል ወንዶች ልጆች አልወለደምን?

ወራሾችስ የሉትምን?

ታዲያ፣ ሚልኮምሸ49፥1 ወይም ንጉሣቸው፤ ዕብራይስጡ መልካም ይላል፤ 3 ይመ። ጋድን ለምን ወረሰ?

የእርሱ ሰዎች ለምን በከተሞቿ ይኖራሉ?

2ስለዚህ በአሞናውያን ከተማ በረባት ላይ፣

የጦርነት ውካታ ድምፅ

የሚሰማበት ጊዜ ይመጣል፤”

ይላል እግዚአብሔር

“እርሷም የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች፤

በዙሪያዋ ያሉት መንደሮችም ይቃጠላሉ፤

እስራኤልም ከአገሯ ያስወጧትን፣

ከአገሯ ታስወጣለች፤”

ይላል እግዚአብሔር

3“ሐሴቦን ሆይ፤ ጋይ ጠፍታለችና ዋይ በይ፤

የራባት ሴቶች ልጆች ሆይ ጩኹ፤

ማቅ ለብሳችሁ አልቅሱ፤

ሚልኮም ከካህናቱና ከመኳንንቱ ጋር፣

ተማርኮ ይወሰዳልና፣

በቅጥር ውስጥ ወዲያ ወዲህ ተሯሯጡ።

4አንቺ ከዳተኛ ልጅ ሆይ፤

በሸለቆችሽ ለምን ትመኪያለሽ?

ለምንስ በፍሬያማ ሸለቆሽ ትኵራሪያለሽ?

በብልጽግናሽ ተማምነሽ፣

‘ማን ሊነካኝ ይችላል?’ ትያለሽ።

5በዙሪያሽ ካሉት ሁሉ ዘንድ፣

ሽብር አመጣብሻለሁ፤”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

“እያንዳንዳችሁ ትሰደዳላችሁ፤

በሽሽት ላይ ያሉትንም የሚሰበስብ አይገኝም።

6“ከዚያ በኋላ ግን፣ የአሞናውያንን ምርኮ እመልሳለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

ስለ ኤዶም የተነገረ መልእክት

49፥9-10 ተጓ ምብ – አብ 5-6

49፥14-16 ተጓ ምብ – አብ 1-4

7ስለ ኤዶም፤

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ጥበብ ከቴማን ጠፍቷልን?

ምክር ከአስተዋዮች ርቋልን?

ጥበባቸውስ ተሟጧልን?

8ዔሳውን በምቀጣ ጊዜ፣

ጥፋት ስለማመጣበት፣

እናንተ በድዳን የምትኖሩ ሆይ፤

ወደ ኋላ ተመልሳችሁ ሽሹ፤ ጥልቅ ጕድጓድ ውስጥ ተደበቁ።

9ወይን ለቃሚዎች ወደ አንተ ቢመጡ፣

ጥቂት ወይን አያስቀሩምን?

ሌቦችስ በሌሊት ቢመጡ፣

የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ብቻ አይደለምን?

10እኔ ግን ዔሳውን አራቍተዋለሁ፤

መደበቅም እንዳይችል፣

መሸሸጊያ ስፍራዎቹን እገልጣለሁ፤

ልጆቹ፣ ዘመዶቹና ጎረቤቶቹ ይጠፋሉ፤

እርሱም ራሱ አይኖርም።

11ወላጆች የሌላቸውን ልጆችህን ተዋቸው፤ እኔ ለሕይወታቸው እጠነቀቃለሁ፤ መበለቶቻችሁም በእኔ ይታመኑ።”

12እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ከጽዋው መጠጣት የማይገባቸው ሊጠጡ ግድ ከሆነ፣ አንተ እንዴት ሳትቀጣ ትቀራለህ? መቀጣትህ አይቀርም፤ መጠጣት ይገባሃል። 13ባሶራ ፈራርሳ የድንጋጤ፣ የመዘባበቻና የርግማን ምልክት እንደምትሆን በራሴ ምያለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ከተሞቿም ሁሉ ለዘላለም ባድማ ይሆናሉ።”

14ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ሰምቻለሁ፤

“እርሷን ለመውጋት ተሰብሰቡ፤

ለጦርነትም ውጡ”

የሚል መልእክተኛ ወደ ሕዝቦች ተልኳል።

15“እነሆ፤ በሕዝቦች መካከል ታናሽ፣

በሰዎችም ዘንድ የተናቅህ አደርግሃለሁ።

16አንተ በዐለት ንቃቃት ውስጥ የምትኖር፣

የተራራውንም ከፍታ የያዝህ ሆይ፤

የምትነዛው ሽብር፣

የልብህም ኵራት አታልሎሃል፤

መኖሪያህን እንደ ንስር በከፍታ ቦታ ብትሠራም፣

ከዚያ ወደ ታች እጥልሃለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

17“ኤዶም የድንጋጤ ምልክት ትሆናለች፤

ከቍስሎቿም ሁሉ የተነሣ፣

በዚያ የሚያልፍ ሁሉ በመደነቅ ያላግጥባታል።

18በዙሪያቸው ካሉት ከተሞች ጋር፣

ሰዶምና ገሞራ እንደ ተገለበጡ፣”

ይላል እግዚአብሔር

እንዲሁ ማንም በዚያ አይኖርም፤

አንድም ሰው አይቀመጥባትም።

19“አንበሳ ከዮርዳኖስ ደኖች፣

ወደ ግጦሽ ሜዳ ብቅ እንደሚል፣

እኔም በኤዶም ላይ ድንገት እወጣለሁ፤ ከምድሩም አባርረዋለሁ።

የመረጥሁትን በእርሱ ላይ እሾማለሁ፤

እንደ እኔ ያለ ማን ነው? ማንስ ሊገዳደረኝ ይችላል?

የትኛውስ እረኛ ሊቋቋመኝ ይችላል?”

20ስለዚህ እግዚአብሔር በኤዶም ላይ ያለውን ዕቅድ፣

በቴማን በሚኖሩትም ላይ ያሰበውን ሐሳብ ስሙ፤

ታናናሹ መንጋ ተጐትቶ ይወሰዳል፤

በእነርሱም ምክንያት መሰማሪያቸውን ፈጽሞ ያጠፋል።

21በውድቀታቸው ድምፅ ምድር ትናወጣለች፤

ጩኸታቸውም እስከ ቀይ ባሕር49፥21 ዕብራይስጡ ያም ሱፍ ይላል፤ ትርጕሙ የሸንበቆ ባሕር ማለት ነው። ያስተጋባል።

22እነሆ፤ እንደ ንስር ተወርውሮ ይወርድባታል፤

ክንፎቹንም በባሶራ ላይ ይዘረጋል፤

በዚያን ቀን የኤዶም ጦረኞች ልብ፣

በምጥ እንደ ተያዘች ሴት ልብ ይሆናል።

ስለ ደማስቆ የተነገረ መልእክት

23ስለ ደማስቆ፣

“ክፉ ወሬ ሰምተዋልና፣

ሐማትና አርፋድ ደንግጠዋል፤

እንደ49፥23 ዕብራይስጡ በተናወጠ ይላል። ተናወጠ ባሕርም ታውከዋል፤

ልባቸውም ቀልጧል።

24ደማስቆ ተዳከመች፤

ትሸሽም ዘንድ ወደ ኋላ ተመለሰች፤

ብርክ ያዛት፣

ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

ጭንቅና መከራ ዋጣት።

25ደስ የምሰኝባት፣

የታወቀችው ከተማ እንዴት ተተወች?

26በርግጥ ወንዶች ወጣቶቿ በየአደባባዩ ይረግፋሉ፤

በዚያ ቀን ወታደሮቿ ሁሉ ይወድቃሉ፤”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

27“በደማስቆ ቅጥር ላይ እሳት እለኵሳለሁ፤

የወልደ አዴርንም ዐምባ ይበላል።”

ስለ ቄዳርና ስለ ሐጾር የተነገረ መልእክት

28የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ስለ ወጋቸው ስለ ቄዳርና ስለ ሐጾር መንግሥታት የተነገረ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ተነሡ፣ ቄዳርን ውጉ፤

የምሥራቅንም ሕዝብ ደምስሱ።

29ድንኳኖቻቸውና መንጎቻቸው ይወሰዳሉ፤

መጠለያቸውና ግመሎቻቸው ሳይቀሩ፣

ከነዕቃዎቻቸው ይነጠቃሉ፤

ሰዎች፣ ‘ሽብር በሽብር ላይ መጥቶባቸዋል፤’

እያሉ ይጮኹባቸዋል።

30በሐጾር የምትኖሩ ሆይ፣

በጥድፊያ ሽሹ፤ በጥልቅ ጕድጓድ ተሸሸጉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በእናንተ ላይ ጠንክሯልና፣

ወረራም ዶልቶባችኋል።

31“ተነሡ፣ ተዘልሎ የተቀመጠውን፣

በራሱ ተማምኖ የሚኖረውን ሕዝብ ውጉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

“መዝጊያና መቀርቀሪያ በሌለው፤

ለብቻው በሚኖረው ሕዝብ ላይ ዝመቱ።

32ግመሎቻቸው ይዘረፋሉ፤

ከብቶቻቸውንም አንጋግተው ይነዱባቸዋል፤

ጠጕሩን የሚቀነብበውን ወገን49፥32 ወይም በሩቅ ስፍራ ያለውን

እበትናለሁ፤ ከየአቅጣጫው መዓት አመጣባችኋለው።”

ይላል እግዚአብሔር

33“ሐጾር የቀበሮዎች መፈንጫ፣

ለዘላለም ባድማ ትሆናለች፤

ማንም በዚያ አይኖርም፤

የሚቀመጥባትም አይገኝም።”

ስለ ኤላም የተነገረ መልእክት

34በይሁዳ ንጉሥ በሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ ላይ ወደ ነቢዩ ወደ ኤርምያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

35የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ የኀያልነቷን መሠረት፣

የኤላምን ቀስት እሰብራለሁ።

36ከአራቱ የሰማይ ማእዘናት፣

በኤላም ላይ አራቱን ነፋሳት አመጣለሁ፤

ወደ አራቱም ነፋሳት እበትናቸዋለሁ፤

ከኤላም የሚማረኩት የማይደርሱበት፣

አገር አይገኝም።

37ነፍሳቸውን በሚሹ ጠላቶቻቸው ፊት፣

ኤላምን አርበደብዳለሁ፤

በላያቸው ላይ መዓትን፣

ይኸውም ቍጣዬን አመጣባቸዋለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

“ፈጽሜ አስካጠፋቸውም ድረስ፣

በሰይፍ አሳድዳቸዋለሁ።

38ዙፋኔን በኤላም እዘረጋለሁ፤

ነገሥታቷንና መኳንንቷን አጠፋለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

39“ነገር ግን የኋላ ኋላ፣

የኤላምን ምርኮ እመልሳለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

耶利米書 49:1-39

審判亞捫的預言

1論到亞捫人,耶和華說:

「難道以色列沒有子孫,

沒有繼承人嗎?

為什麼祭拜米勒公的人佔據了迦得,住在城邑中?」

2耶和華說:

「看啊,時候將到,

我要使亞捫人的拉巴城外響起戰爭的呐喊。

拉巴必淪為廢墟,

它周圍的鄉村都要被焚燒,

以色列人必收復失地。

這是耶和華說的。

3希實本啊,哀哭吧!

因為城毀滅了。

拉巴的居民啊,痛哭吧!

披上麻衣悲傷地在城牆內跑來跑去吧!

因為米勒公及其祭司和官長都要被擄走。

4背叛的人民啊,

你們為肥沃的山谷而感到自豪嗎?

你們依仗財富以為無人敢來侵犯。」

5上帝——萬軍之耶和華說:

「看啊,我要使你們四面受敵,

驚恐萬狀,四散奔逃,

潰不成軍。

6然而,日後我要使被擄的亞捫人重建家園。

這是耶和華說的。」

審判以東的預言

7論到以東,萬軍之耶和華說:

提幔再沒有智者了嗎?

謀士已無計可施了嗎?

他們都失去智慧了嗎?

8底但的居民啊,

你們要轉身逃命,

藏在深洞裡,

因為我必降災禍懲罰以東

9人們來以東摘葡萄,不會摘盡;

盜賊夜間來偷東西,不會偷光。

10但我要奪走以東人所有的一切,

我要使他們無處藏身。

他們及其孩子、弟兄和鄰居必一同滅亡。

11撇下你們的孤兒吧!

我必使他們存活;

你們的寡婦也可以倚靠我。」

12耶和華說:「看啊,那些本不該喝這杯憤怒的人尚且要喝,更何況你們呢?你們必難逃懲罰,你們一定要喝這杯憤怒。 13因為我已憑自己起誓,波斯拉必淪為廢墟,令人驚懼,被人嘲笑和咒詛。它周圍的村鎮要永遠荒涼。這是耶和華說的。」

14我從耶和華那裡聽到消息,

有位使者被派去聯合列國來攻打以東

15耶和華說:

以東啊,我要使你在列國中成為被藐視的弱國。

16你這棲身在石縫間、盤踞在高山上的民族啊,

你令人驚懼、心高氣傲,

其實只是自欺。

儘管你像老鷹在高處搭窩,

我也必把你拉下來。

這是耶和華說的。

17以東的下場將很可怕,它的滿目瘡痍令路人驚懼、嗤笑。 18那裡要像所多瑪蛾摩拉及其周圍的村鎮一樣被毀滅,荒無人煙。這是耶和華說的。 19看啊,我必在瞬間把以東人趕離家園,如約旦河邊叢林中跳出的獅子趕散草場的羊群。我要派我揀選的人統治這地方。誰能與我相比?誰能與我較量?哪位首領能抵擋我?」 20因此,你們要聽聽耶和華攻擊以東的策略,聽聽祂攻擊提幔居民的計劃。他們的孩子要被拖走,他們的家園要被毀滅。 21以東傾覆的聲音震動大地,哭喊聲直傳到海。 22看啊,敵人必像展翅飛來的鷹一樣攻擊波斯拉。到那日,以東的勇士必像臨盆的婦女一樣膽戰心驚。

審判大馬士革的預言

23論到大馬士革,耶和華說:

哈馬亞珥拔驚恐不安,

因為他們聽見了壞消息。

他們心驚膽戰,像大海一樣無法平靜。

24大馬士革喪失勇氣,轉身逃命。

她像分娩的婦人一樣驚恐不安,

充滿痛苦和憂愁。

25我所喜悅的名城為何還沒有被撇棄?

26城中的青年將倒斃街頭,

那時所有的戰士都要滅亡。

這是萬軍之耶和華說的。

27我要焚燒大馬士革的城牆和便·哈達的宮殿。」

審判基達和夏瑣的預言

28論到被巴比倫尼布甲尼撒打敗的基達夏瑣的各城邦,耶和華說:

迦勒底人啊,去攻打基達

消滅那些東方人吧!

29你們要搶走他們的帳篷、

幔子、器皿、羊群和駱駝。

他們必聽見呼喊聲,

『真恐怖!四面都是敵人。』

30夏瑣的居民啊,快逃命吧!

逃得遠遠的藏起來,

因為巴比倫尼布甲尼撒已計劃攻擊你們,

準備消滅你們。

這是耶和華說的。

31迦勒底人啊,

上去攻打那安逸無憂、無門無閂、獨居一方的國家吧!

這是耶和華說的。

32他們的駱駝必被擄去,

大群的牲畜必成為戰利品。

我要把剃去鬢髮的人驅散到四方,

使災禍從四面八方臨到他們。

這是耶和華說的。

33夏瑣要永遠荒涼,

杳無人跡,

成為豺狼出沒的地方。」

審判以攔的預言

34猶大西底迦執政初期,耶和華告訴了耶利米先知有關以攔的事。 35萬軍之耶和華說:「看啊,我要摧毀以攔的弓箭手——他們的精銳之師。 36我要使敵人從四面八方如風而來,把以攔人驅散到四方,使他們流落到列國。 37我要讓仇敵擊潰他們,我要發烈怒降禍給他們,用刀劍追殺他們,直到徹底消滅他們。這是耶和華說的。 38我要在以攔設立我的寶座,消滅那裡的君王和官長。這是耶和華說的。 39但將來有一天,我要使被擄的以攔人重建家園。這是耶和華說的。」