ኤርምያስ 27 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 27:1-22

የይሁዳ በናቡከደነፆር ሥር መውደቅ

1በይሁዳ ንጉሥ፣ በኢዮስያስ ልጅ በሴዴቅያስ27፥1 ጥቂት የዕብራይስጥ ጽሑፎችና የሱርሰት ትርጕም (ኤር 27፥312 እና 28፥1 ይመ)፣ አንዳንድ የዕብራይስጥ ጽሑፎች ኢዮአቄም ይላሉ (አብዛኛዎቹ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ይህ ጥቅስ ቍጥር የላቸውም)። ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ ላይ ይህ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ መጣ፤ 2እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “የዕንጨት ቀንበር ሠርተህ በጠፍር ማነቆ አያይዘውና በዐንገትህ አስገባው፤ 3ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሴዴቅያስ፣ ወደ ኢየሩሳሌም በመጡት ሰዎች በኩል ለኤዶም፣ ለሞዓብ፣ ለአሞን፣ ለጢሮስና ለሲዶና ነገሥታት መልእክት ላክ። 4ለጌቶቻቸውም እንዲያሳውቁ እንዲህ ብለህ ንገራቸው፤ ‘የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ለጌቶቻችሁ ይህን ንገሯቸው፤ 5በታላቁ ኀይሌና በተዘረጋው ክንዴ ምድርን፣ በላይዋ የሚኖሩትን ሰዎችና እንስሳት ፈጥሬአለሁ፤ ለምወድደውም እሰጣለሁ። 6አሁንም እነዚህን አገሮች ሁሉ ለአገልጋዬ ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር አሳልፌ እሰጣለሁ፤ የዱር አራዊት እንኳ እንዲገዙለት አደርጋለሁ። 7የእርሱ አገር በተራው ለሌሎች እስከሚገዛበት ጊዜ ድረስ፣ ሕዝቦች ሁሉ ለእርሱ፣ ለልጁና ለልጅ ልጁ ይገዛሉ፤ በዚያን ጊዜ ብዙ ሕዝቦችና ታላላቅ ነገሥታት እርሱን ይገዙታል።

8“ ‘ “ነገር ግን ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር የማይገዛ፣ ዐንገቱንም ከቀንበሩ በታች ዝቅ የማያደርግ ማንኛውንም ሕዝብ ወይም መንግሥት በእጁ እስከማጠፋው ድረስ በሰይፍና በራብ፣ በመቅሠፍትም እቀጣዋለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር9ስለዚህ፣ ‘የባቢሎንን ንጉሥ አታገለግሉም’ የሚሏችሁን ነቢያታችሁን፣ ሟርተኞቻችሁን፣ ሕልመኞቻችሁን፤ መናፍስት ጠሪዎቻችሁንና መተተኞቻቸሁን አትስሙ፤ 10ከምድራችሁ እንድትፈናቀሉ፣ እኔም እንዳሳድዳችሁና እንዳጠፋችሁ የሐሰት ትንቢት ይነግሯችኋልና። 11ነገር ግን ከባቢሎን ንጉሥ ቀንበር በታች ዐንገቱን ዝቅ የሚያደርገውንና የሚያገለግለውን ማንኛውንም ሕዝብ በገዛ ምድሩ እንዲቀርና እያረሰም በዚያ እንዲኖር አደርገዋለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር።” ’ ”

12ለይሁዳ ንጉሥ ለሴዴቅያስም ይህንኑ መልእክት እንዲህ ብዬ ነገርሁት፤ “ዐንገታችሁን ከባቢሎን ንጉሥ ቀንበር በታች ዝቅ አድርጉ፤ እርሱንና ሕዝቡን አገልግሉ፤ በሕይወትም ትኖራላችሁ። 13አንተና ሕዝብህ፣ እግዚአብሔር ለባቢሎን ንጉሥ አልገዛም ያለውን ሕዝብ ባስጠነቀቀበት በሰይፍ፣ በራብና በመቅሠፍት ለምን ታልቃላችሁ? 14ሐሰተኛ ትንቢት ስለሚነግሯችሁ፣ ‘የባቢሎንን ንጉሥ አታገለግሉም’ የሚሏችሁን ነቢያት አትስሙ፤ 15‘እኔ አልላክኋቸውም’ ይላል እግዚአብሔር ‘የሐሰት ትንቢት በስሜ ይናገራሉ፤ ስለዚህ እናንተንና ትንቢት የሚናገሩላችሁን ነቢያት አሳድዳለሁ፤ እናንተም ትጠፋላችሁ።’ ”

16እኔም ለካህናቱና ለዚህ ሕዝብ ሁሉ እንዲህ አልሁ፤ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የእግዚአብሔር ቤት ዕቃ ከባቢሎን ቶሎ ይመለሳል’ የሚሏችሁን ነቢያት አትስሟቸው፤ የሚነግሯችሁ የሐሰት ትንቢት ነውና። 17ስለዚህ እነርሱን መስማት ትታችሁ ለባቢሎን ንጉሥ ተገዙ፤ በሕይወትም ትኖራላችሁ፤ ባለመታዘዛችሁስ ይህች ከተማ ለምን ትፈራርስ? 18እውነተኞች ነቢያት ከሆኑና በርግጥ የእግዚአብሔር ቃል ካላቸው፣ በእግዚአብሔር ቤትና በይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት በኢየሩሳሌምም የቀሩት ዕቃዎች ወደ ባቢሎን እንዳይወሰዱ ወደ ሰራዊት ጌታ ወደ እግዚአብሔር እስቲ ይማልዱ! 19የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በዚህች ከተማ ስለ ቀሩት ዐምዶች፣ ከናስ ስለ ተሠራው ትልቁ ገንዳ፣ ስለ ተንቀሳቃሽ ማስቀመጫዎችና ስለ ሌሎቹም ዕቃዎች እንዲህ ይላልና፤ 20የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር የይሁዳን ንጉሥ የኢዮአቄምን ልጅ ኢኮንያንን፣27፥20 ኢኮንያን የኢዮአኪን ሌላው አቻ ስም ነው። ከኢየሩሳሌምና ከይሁዳ መኳንንት ጋር ማርኮ ወደ ባቢሎን በወሰደ ጊዜ እነዚህ በከተማዪቱ የቀሩ ዕቃዎች ስለሆኑ፣ 21በእግዚአብሔር ቤትና በይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት በኢየሩሳሌምም ስለ ቀሩት ዕቃዎች፣ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ 22‘ወደ ባቢሎን ይወሰዳሉ፤ እስከምጐበኛቸውም ቀን ድረስ በዚያ ይቀመጣሉ’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘በዚያ ጊዜም እመልሳቸዋለሁ፤ ወደዚህም ስፍራ አመጣቸዋለሁ።’ ”

New International Reader’s Version

Jeremiah 27:1-22

Judah Will Serve Nebuchadnezzar

1A message from the Lord came to Jeremiah. It was shortly after Zedekiah became king of Judah. He was the son of Josiah. 2The Lord said, “Make a yoke out of ropes and wooden boards. Put it on your neck. 3Then write down a message for the kings of Edom, Moab, Ammon, Tyre and Sidon. Give it to their messengers who have come to Jerusalem. They have come to see Zedekiah, the king of Judah. 4Give them a message for the kings who sent them. It should say, ‘The Lord who rules over all is the God of Israel. He says, “Here is what I want you to tell your masters. 5I reached out my great and powerful arm. I made the earth. I made its people and animals. And I can give the earth to anyone I please. 6Now I will hand over all your countries to my servant Nebuchadnezzar. He is the king of Babylon. I will put even the wild animals under his control. 7All the nations will serve him and his son and grandson. After that, I will judge his land. Then many nations and great kings will make him serve them.

8“ ‘ “But suppose any nation or kingdom will not serve Nebuchadnezzar, the king of Babylon. And suppose it refuses to put its neck under his yoke. Then I will punish that nation with war, hunger and plague,” announces the Lord. “I will punish it until his powerful hand destroys it. 9So do not listen to your prophets. Do not listen to those who claim to have secret knowledge. Do not listen to those who try to explain your dreams. Do not listen to those who get messages from people who have died. Do not listen to those who practice evil magic. All of them will tell you, ‘You won’t serve the king of Babylon.’ 10But they prophesy lies to you. If you listen to them, you will be removed far away from your lands. I will drive you away from them. And you will die. 11But suppose any nation will put its neck under the yoke of the king of Babylon. And suppose it serves him. Then I will let that nation remain in its own land. I will let its people plow the land and live there,” ’ ” announces the Lord.

12I gave the same message to Zedekiah, the king of Judah. I said, “Put your neck under the yoke of the king of Babylon. Obey him. Serve his people. Then you will live. 13Why should you and your people die? Why should you die of war, hunger and plague? That’s what the Lord said would happen to any nation that won’t serve the king of Babylon. 14Don’t listen to the words of the prophets who say to you, ‘You won’t serve the king of Babylon.’ They are prophesying lies to you. 15‘I have not sent them,’ announces the Lord. ‘They are prophesying lies in my name. So I will drive you away from your land. And you will die. So will the prophets who prophesy to you.’ ”

16Then I spoke to the priests and all these people. I said, “The Lord says, ‘Do not listen to the prophets who speak to you. They say, “Very soon the objects from the Lord’s house will be brought back from Babylon.” Those prophets are prophesying lies to you. 17Do not listen to them. Serve the king of Babylon. Then you will live. Why should this city be destroyed? 18If they are prophets and have received a message from me, let them pray to me. I am the Lord who rules over all. Those prophets should pray that what is still in Jerusalem will remain here. They should pray that the objects in my house and the king’s palace will not be taken to Babylon. 19I am the Lord who rules over all. Do you know what these objects are? They include the two pillars in front of the temple. They include the huge bronze bowl. They include the bronze stands that can be moved around. And they include the other things left in this city. 20Nebuchadnezzar, the king of Babylon, did not take these things away at first. That was when he took King Jehoiachin from Jerusalem to Babylon. Jehoiachin is the son of Jehoiakim. Nebuchadnezzar also took all the nobles of Judah and Jerusalem along with Jehoiachin. 21I am the Lord who rules over all. I am the God of Israel. Here is what will happen to the things that are left in my house, the king’s palace and Jerusalem. 22They will be taken to Babylon. They will remain there until the day I come for them,’ announces the Lord. ‘Then I will bring them back. I will return them to this place.’ ”