ኤርምያስ 1 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 1:1-19

1የኬልቅያስ ልጅ፣ ኤርምያስ የተናገረው ቃል ይህ ነው፤ አባቱ በብንያም አገር በዓናቶት ከሚገኙት ካህናት አንዱ ነበረ። 2የእግዚአብሔር ቃል የይሁዳ ንጉሥ፣ የአሞን ልጅ ኢዮስያስ በነገሠ በዐሥራ ሦስተኛው ዓመት ወደ ኤርምያስ መጣ፤ 3ደግሞም በይሁዳ ንጉሥ፣ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ንግሠ ዘመን፤ እንዲሁም በይሁዳ ንጉሥ፣ በኢዮስያስ ልጅ በሴዴቅያስ ንግሠ ዘመን፤ እስከ ዐሥራ አንደኛው ዓመት መጨረሻ ድረስ የኢየሩሳሌም ሕዝብ ተማርኮ እስከ ሄደበት እስከ አምስተኛው ወር ድረስ ወደ እርሱ ይመጣ ነበር።

የኤርምያስ መጠራት

4የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ መጣ፤ እንዲህም አለኝ፤

5“በማሕፀን ሳልሠራህ ዐወቅሁህ፤

ከመወለድህ በፊት ለየሁህ፤1፥5 ወይም መረጥሁህ

ለሕዝቦችም ነቢይ እንድትሆን ሾምሁህ።”

6እኔም፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንዴት እንደምናገር አላውቅም፤ ገና ሕፃን ልጅ ነኝና” አልሁ።

7እግዚአብሔር ግን እንዲህ አለኝ፤ “ ‘ገና ሕፃን ልጅ ነኝ’ አትበል፤ ወደምልክህ ሁሉ ሄደህ፣ ያዘዝሁህን ሁሉ ትናገራለህ፤ 8እኔ አድንህ ዘንድ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራቸው” ይላል እግዚአብሔር

9እግዚአብሔርም እጁን ዘርግቶ አፌን ዳሰሰና እንዲህ አለኝ፤ “እነሆ፤ ቃሌን በአፍህ አኑሬአለሁ፤ 10እንግዲህ፣ እንድትነቅልና እንድታፈርስ፣ እንድታጠፋና እንድትገለብጥ፣ እንድታንጽና እንድትተክል በአሕዛብና በመንግሥታት ላይ ዛሬ ሾምሁህ።”

11የእግዚአብሔር ቃል፣ “ኤርምያስ ሆይ፣ ምን ታያለህ?” ሲል ወደ እኔ መጣ።

እኔም፣ “የለውዝ በትር አያለሁ” አልሁ።

12እግዚአብሔርም፣ “ትክክል አይተሃል፤ ቃሌን እፈጽመው ዘንድ እተጋለሁና”1፥12 እተጋለሁ ለሚለው የዕብራይስጡ አነባበብ የለውዝ በትር ከሚለው ጋር ይመሳሰላል። አለኝ።

13ዳግመኛም የእግዚአብሔር ቃል፣ “ምን ታያለህ?” ሲል ወደ እኔ መጣ።

እኔም፣ “አንድ የሚፈላ ማሰሮ አያለሁ፤ አፉም ከሰሜን ወደዚህ ያዘነበለ ነው” አልሁ።

14እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “ከሰሜን በምድሪቱ በሚኖሩ ሁሉ ላይ ድንገት መዓት ይወርድባቸዋል። 15እነሆ፤ የሰሜን መንግሥታትን ሕዝቦች ሁሉ እጠራለሁ” ይላል እግዚአብሔር

“ንጉሦቻቸው ይመጣሉ፤

ዙፋናቸውን በኢየሩሳሌም መግቢያ በሮች፣

በቅጥሮቿ ዙሪያ ሁሉ፣

በይሁዳም ከተሞች ሁሉ ይዘረጋሉ።

16እኔን በመተው ክፋት ስለ ሠሩ፣

ለሌሎች አማልክት ዕጣን ስላጠኑ፣

እጆቻቸው የሠሯቸውን ስላመለኩ፣

በሕዝቤ ላይ ፍርድን ዐውጄአለሁ።

17“አንተ ግን ወገብህን ታጠቅ፤ ተነሥተህም ያዘዝሁን ሁሉ ንገራቸው፤ አትፍራቸውም፤ አለዚያ በፊታቸው አስፈራሃለሁ። 18እነሆ፤ ዛሬ በመላዪቱ ምድር ላይ አስነሣሃለሁ፤ ይኸውም የይሁዳን ነገሥታት፣ አለቆቿን፣ ካህናቷንና የምድሪቱን ሕዝብ ሁሉ መቋቋም እንድትችል የተመሸገ ከተማ፣ የብረት ምሰሶና የናስ ቅጥር አድርጌሃለሁ። 19ይዋጉሃል፤ ዳሩ ግን አድንህ ዘንድ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አያሸንፉህም” ይላል እግዚአብሔር

Japanese Contemporary Bible

エレミヤ書 1:1-19

1

1ここに書いてあるのは、ユダのベニヤミンの地のアナトテという町にいた祭司、ヒルキヤの子エレミヤに与えられた神のことばです。 2ユダ王国のアモンの子、ヨシヤ王の治世第十三年に最初のことばがありました。 3そののち、ヨシヤの子、エホヤキム王の時代、ヨシヤの子、ゼデキヤ王の治世第十一年の七月にエルサレムが陥落し、住民が捕囚として連れ去られるまで、数回にわたって神のことばがありました。

エレミヤの召命

4主は私に、こう語りました。

5「わたしは、母の胎内に宿る前から

おまえを知っていた。

生まれる前から、

わたしの聖なる者として取っておき、

国々にわたしのことばを伝える者に任命していた。」

6「神よ、とんでもないことです。

私にできるはずがありません。

若すぎて、何を語ればよいのかわかりません。

7「そんなことを言ってはならない。

わたしが送り出す所どこへでも行き、

命じることはすべて語るのだ。

8人を恐れてはいけない。

主であるわたしがついていて、

どんな時にも助けるのだから。」

9こう言ってから、神は私の口に触れました。

「わたしのことばをおまえの口に授けた。

10今日から、世界の国々に警告する仕事が始まる。

おまえの口から語られるわたしのことばどおりに、

ある国を引き倒し、滅ぼし、

ある国は起こし、育て、大国にする。」

11それから、主はこう尋ねられました。「エレミヤよ、何が見えるか。」「アーモンドの枝でできたむちです。」 12「そのとおりだ。それは、わたしが必ず恐ろしい罰を下すしるしだ。

13今度は何が見えるか。」「煮立っているなべが南の方に傾き、煮え湯がユダの上にこぼれていくのが見えます。」

14「そのとおりだ。

北からの恐怖が、全住民に降りかかる。

15わたしは北方の国々の軍隊に、

エルサレムを攻めさせる。

彼らは都の門と城壁沿いに、

またユダのほかの町々に、それぞれの王座を作る。

16こうして、わたしの民に罰を加える。

わたしを捨て、

自分の手で作った神々を拝んだからだ。

17さあ、身じたくを整えて出かけなさい。

わたしが伝えることをすべて語るのだ。

彼らを怖がるな。

恐れるなら、彼らの目の前でおまえを

もの笑いの種にする。

18わたしは今日、

おまえを彼らにはたち打ちできない者とした。

彼らはどうしても、

おまえに危害を加えることができない。

おまえは、難攻不落の町のように

がんじょうそのもので、

鉄の柱、青銅の重い門のように強い。

王たち、将校たち、祭司たちをはじめ、

この国の民は、おまえと戦っても、

とうてい勝ち目がない。

19攻撃をしかけても、途中であきらめる。

わたしがおまえと共にいて、必ず救い出すからだ。」