ኢዮብ 7 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 7:1-21

1“የሰው ሕይወት በምድር ላይ ብርቱ ተጋድሎ አይደለምን?

ዘመኑስ እንደ ምንደኛ ዘመን አይደለምን?

2የምሽትን ጥላ እንደሚመኝ አገልጋይ፣

ደመወዙንም እንደሚናፍቅ ምንደኛ፣

3እንዲሁ ከንቱ ወራት ታደሉኝ፣

የጕስቍልና ሌሊቶችም ተወሰኑልኝ።

4በተኛሁ ጊዜ ‘መቼ ነግቶ እነሣለሁ?’

እላለሁ፤ ሌሊቱ ይረዝማል፤ እስኪነጋም እገላበጣለሁ።

5አካሌ ቈስሎ ትልና ቅርፊት ለብሷል፤

ቈዳዬ አፈክፍኳል፤ ቍስሌም አመርቅዟል።

6“ዘመኔ ከሸማኔ መወርወሪያ ይልቅ ይፈጥናል፤

ያለ ተስፋም ያልቃል።

7ሕይወቴ ትንፋሽ ያህል እንደ ሆነች ዐስብ፤

ዐይኔም ከእንግዲህ ደስታን አያይም።

8አሁን የሚያየኝ ሰው ዐይን ከእንግዲህ አያየኝም፤

ትፈልገኛለህ፤ እኔ ግን የለሁም።

9ደመና በንኖ እንደሚጠፋ፣

ወደ መቃብር7፥9 የዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። የሚወርድም አይመለስም።

10ወደ ቤቱ ዳግመኛ አይመለስም፤

ስፍራውም ከእንግዲህ አያውቀውም።

11“ስለዚህ ከቶ ዝም አልልም፤

በመንፈሴ ጭንቀት እናገራለሁ፤

በነፍሴም ምሬት አጕረመርማለሁ።

12በላዬ ጠባቂ ታደርግ ዘንድ፣

እኔ ባሕር ነኝን ወይስ የባሕር አውሬ?

13ዐልጋዬ ያጽናናኛል፣

መኝታዬም ማጕረምረሜን ይቀንስልኛል ባልሁ ጊዜ፣

14አንተ በሕልም ታስፈራራኛለህ፤

በራእይም ታስደነግጠኛለህ፤

15ስለዚህ እንዲህ ሆኖ ከመኖር፣

መታነቅና መሞትን እመርጣለሁ።

16ሕይወቴን እጸየፋለሁ፤ ዘላለም መኖር አልፈልግም፤

ዘመኔ እንደ እስትንፋስ ነውና ተወኝ።

17“ከፍ ከፍ ታደርገው ዘንድ፣

ልብህንም ትጥልበት ዘንድ ሰው ምንድን ነው?

18በየማለዳው ትመረምረዋለህ፤

በየጊዜውም ትፈትነዋለህ።

19ዐይንህን ከእኔ ላይ አታነሣምን?

ምራቄን እንኳ እስክውጥ ፋታ አትሰጠኝምን?

20ሰውን የምትከታተል ሆይ፤

ኀጢአት ብሠራ፣ አንተን ምን አደርግሃለሁ?

ለምን ዒላማህ አደረግኸኝ?

ለምንስ ሸክም ሆንሁብህ?7፥20 ጥቂት የማሶሬቲክ ጽሑፍ ቅጆች፣ የጥንት የዕብራውያን ጸሓፍት ትውፊትና ሰብዓ ሊቃናት እንዲሁ ሲሆኑ፣ አብዛኛው የማሶሬቲክ ጽሑፍ ቅጆች ግን ለራሴ ሸክም ሆንሁ ይላሉ።

21መተላለፌን ለምን ይቅር አትልም?

ኀጢአቴንስ ለምን አታስወግድልኝም?

ትቢያ ውስጥ የምጋደምበት ጊዜ ደርሷል፤

ትፈልገኛለህ፤ እኔ ግን የለሁም።”

Ketab El Hayat

أيوب 7:1-21

1أَلَيْسَتْ حَيَاةُ الإِنْسَانِ جِهَاداً شَاقّاً عَلَى الأَرْضِ، وَأَيَّامُهُ كَأَيَّامِ الأَجِيرِ؟ 2فَكَمَا يَتَشَوَّقُ الْعَبْدُ إِلَى الظِّلِّ، وَالأَجِيرُ يَرْتَقِبُ أُجْرَتَهُ، 3هَكَذَا كُتِبَتْ عَلَيَّ أَشْهُرُ سُوءٍ، وَلَيَالِي شَقَاءٍ قُدِّرَتْ لِي. 4إِذَا رَقَدْتُ أَتَسَاءَلُ: مَتَى أَقُومُ؟ وَلَكِنَّ اللَّيْلَ طَوِيلٌ، وَأَشْبَعُ قَلَقاً إِلَى الصَّبَاحِ. 5اكْتَسَى لَحْمِي بِالدُّودِ وَحَمْأَةِ التُّرَابِ، وَجِلْدِي تَشَقَّقَ وَتَقَرَّحَ. 6أَيَّامِي أَسْرَعُ مِنْ مَكُّوكِ النَّسَّاجِينَ، تَتَلاشَى مِنْ غَيْرِ رَجَاءٍ!

7فَاذْكُرْ يَا اللهُ أَنَّ حَيَاتِي لَيْسَتْ سِوَى نَسَمَةٍ، وَأَنَّ عَيْنَيَّ لَنْ تَعُودَا تَرَيَانِ الْخَيْرَ. 8إِنَّ عَيْنَ مَنْ يَرَانِي الآنَ لَنْ تُبْصِرَنِي فِيمَا بَعْدُ، وَتَلْتَفِتُ عَيْنَاكَ إِلَيَّ فَلا تَجِدَانِنِي بَعْدُ. 9كَمَا يَضْمَحِلُّ السَّحَابُ وَيَزُولُ، هَكَذَا الْمُنْحَدِرُ إِلَى الْهَاوِيَةِ لَا يَصْعَدُ، 10لَا يَرْجِعُ بَعْدُ إِلَى مَنْزِلِهِ، وَمَكَانُهُ لَا يَعْرِفُهُ بَعْدُ. 11لِذَلِكَ لَنْ أُلْجِمَ فَمِي، وَسَأَتَكَلَّمُ مِنْ عُمْقِ عَذَابِ رُوحِي، وَأَشْكُو فِي مَرَارَةِ نَفْسِي. 12أَبَحْرٌ أَنَا أَمْ تِنِّينٌ، حَتَّى أَقَمْتَ عَلَيَّ حَارِساً؟ 13إِنْ قُلْتُ: إِنَّ فِرَاشِي يُعَزِّينِي وَمَرْقَدِي يُزِيلُ كُرْبَتِي، 14فَأَنْتَ تُرَوِّعُنِي بِالأَحْلامِ وَتُرْهِبُنِي بِالرُّؤَى. 15لِذَلِكَ فَضَّلْتُ الاخْتِنَاقَ وَالْمَوْتَ عَلَى جَسَدِي هَذَا. 16كَرِهْتُ حَيَاتِي، فَلَنْ أَحْيَا إِلَى الأَبَدِ، فَكُفَّ عَنِّي لأَنَّ أَيَّامِي نَفْخَةٌ. 17مَنْ هُوَ الإِنْسَانُ حَتَّى تَعْتَبِرَهُ وَتُعِيرَهُ كُلَّ اهْتِمَامٍ؟ 18تَفْتَقِدُهُ فِي كُلِّ صَبَاحٍ وَتَمْتَحِنُهُ فِي كُلِّ لَحْظَةٍ؟ 19حَتَّى مَتَى لَا تُحَوِّلُ وَجْهَكَ عَنِّي، وَتَكُفُّ رَيْثَمَا أَبْلَعُ رِيقِي؟ 20إِنْ أَخْطَأْتُ فَمَاذَا أَفْعَلُ لَكَ يَا رَقِيبَ النَّاسِ؟ لِمَاذَا جَعَلْتَنِي هَدَفاً لَكَ؟ لِمَاذَا جَعَلْتَنِي حِمْلاً عَلَى نَفْسِي؟ 21لِمَاذَا لَا تَصْفَحُ عَنْ إِثْمِي وَتُزِيلُ ذَنْبِي، لأَنَّنِي الآنَ أَرْقُدُ فِي التُّرَابِ، وَعِنْدَمَا تَبْحَثُ عَنِّي أَكُونُ قَدْ فَنِيتُ».