ኢዮብ 41 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 41:1-34

1“ሌዋታንን41፥1 ምናልባት ዐዞ ሊሆን ይችላል። በመንጠቆ ልታወጣው፣

ወይም ምላሱን በገመድ ልታስረው ትችላለህን?

2መሰነጊያ በአፍንጫው ልታስገባ፣

ወይም ጕንጩን በሜንጦ ልትበሳ ትችላለህን?

3እርሱ እንድትምረው ይለማመጥሃል?

በለስላሳ ቃላትስ ይናገርሃል?

4ለዘላለም ባሪያ ታደርገው ዘንድ፣

ከአንተ ጋር ይዋዋላልን?

5እንደ ወፍ አልምደኸው ከእርሱ ጋር ልትጫወት ትችላለህ?

ወይስ ለሴት አገልጋዮችህ መጫወቻነት ታስረዋለህን?

6ነጋዴዎችስ በእርሱ ላይ ይከራከራሉን?

ለቸርቻሪዎችስ ያከፋፍሉታል?

7ቈዳው ላይ ዐንካሴ ልትሰካ፣

ጭንቅላቱንም በዓሣ መውጊያ ጦር ልትበሳ ትችላለህን?

8እርሱን እስቲ ንካው፣

ግብግቡን ታስታውሳለህ፤ ከቶም አያላምድህም።

9እርሱን በቍጥጥር ሥር አውላለሁ ማለት ዘበት ነው፤

በዐይን ማየት እንኳ ብርክ ያስይዛል።

10ሊቀሰቅሰው የሚደፍር የለም፤

ማን ፊቱ ሊቆም ይችላል?

11ነክቶት በሰላም የሚሄድ ማን ነው?

ከሰማይ በታች ማንም የለም።41፥11 አንዳንድ ትርጕሞች፣ በዕዳ የሚጠይቀኝ ማን ነው? ከሰማይ በታች ያለው ሁሉ ንብረቴ ነው ይላሉ።

12“ስለ ብርታቱና ስለ አካላቱ ውበት፣

ስለ እጅና እግሩ ከመናገር አልቈጠብም።

13የደረበውን ልብስ ማን ሊያወልቅ ይችላል?

ማንስ ሊለጕመው ወደ መንጋጋው ይቀርባል?

14አስፈሪ ጥርሶቹ የተገጠገጡበትን፣

የአፉን ደጅ ማን ደፍሮ ይከፍታል?

15ጀርባው፣ አንድ ላይ የተጣበቁ፣

የጋሻ ረድፎች አሉት፤

16እጅግ የተቀራረቡ ስለሆኑ፣

ነፋስ በመካከላቸው አያልፍም፤

17እርስ በርስ የተገጣጠሙ ናቸው፤

አንዱ ከአንዱ ጋር ተጣብቋልና ማንም ሊለያያቸው አይችልም።

18እንጥሽታው የብርሃን ብልጭታ ያወጣል፤

ዐይኖቹም እንደ ማለዳ ጮራ ናቸው።

19ከአፉ ፍም ይወጣል፤

የእሳት ትንታግ ይረጫል።

20በሸንበቆ ማገዶ ላይ ከተጣደ ድስት እንደሚወጣ እንፋሎት፣

ከአፍንጫው ጢስ ይትጐለጐላል።

21እስትንፋሱ ከሰል ያቀጣጥላል፤

የእሳትም ነበልባል ከአፉ ይወጣል።

22ብርታት በዐንገቱ ውስጥ አለ፤

አሸባሪነትም በፊቱ እመር እመር ይላል።

23የሥጋው ንብርብር እርስ በርስ የተጣበቀ፣

በላዩ የጸናና ከቦታው የማይናጋ ነው።

24ደረቱ እንደ ዐለት የጠጠረ፣

እንደ ወፍጮ ድንጋይም የጠነከረ ነው።

25እርሱ በተነሣ ጊዜ፣ ኀያላን ይርዳሉ፤

በሚንቀሳቀስበትም ጊዜ ወደ ኋላ ያፈገፍጋሉ።

26ጦር፣ ፍላጻ ወይም ዐንካሴ፣

ሰይፍም ቢያገኘው አንዳች አይጐዳውም።

27እርሱ ብረትን እንደ አገዳ፣

ናስንም እንደ ነቀዘ ዕንጨት ይቈጥራል።

28ቀስት አያባርረውም፤

የወንጭፍ ድንጋይም ለእርሱ እንደ ገለባ ነው።

29ቈመጥ በእርሱ ፊት እንደ ገለባ ነው፤

ጦር ሲሰበቅ ይሥቃል።

30የሆዱ ሥር እንደ ሸካራ ገል ነው፤

እንደ መውቂያ መሣሪያም በጭቃ ላይ ምልክት ጥሎ ያልፋል።

31እንደሚፈላ ምንቸት ጥልቁን ያናውጠዋል፤

ባሕሩንም እንደ ሽቶ ብልቃጥ ያደርገዋል።

32ያለፈበትን መንገድ ብሩህ ያደርጋል፤

ቀላዩንም ሽበት ያወጣ ያስመስለዋል።

33ያለ ፍርሀት የተፈጠረ፣

እንደ እርሱ ያለ በምድር ላይ የለም።

34ከፍ ያሉትን ሁሉ በንቀት ይመለከታል፤

በትዕቢተኞችም ሁሉ ላይ ንጉሥ ነው።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 41:1-34

1“你岂能用鱼钩钓鳄鱼,

用绳索绑住它的舌头?

2你岂能用绳子穿它的鼻子,

用钩子穿它的腮骨?

3它岂会向你连连求饶,

对你说柔和的话?

4它岂肯与你立约,

一生做你的奴隶?

5你岂能拿它当小鸟玩耍,

或拴起来给幼女取乐?

6渔夫们岂能把它当货物出售,

卖给商人?

7你岂能在它皮上戳满长矛,

头上插满鱼叉?

8你动手碰碰它,

就知道有何恶战,绝不会再碰。

9企图捕捉它的都会失望,

人看到它就会心惊胆战。

10再凶猛的人也不敢惹它。

这样,谁能在我面前站立得住?

11谁给过我什么,要我偿还?

天下万物都是我的。

12“论到它的四肢、大力和姣美的身体,

我不能缄默不言。

13谁能剥去它的外皮?

谁能给它戴上辔头?

14谁能打开它的口?

它的牙齿令人恐惧。

15它的脊背覆着行行鳞甲,

牢牢地密封在一起,

16紧密无间,

连气也透不进去。

17鳞甲彼此相连相扣,

无法分开。

18它打喷嚏时,水光四射;

它的眼睛发出晨光;

19口中喷出火炬,

迸出火星;

20鼻孔冒烟,

如沸腾的锅和燃烧的芦苇;

21呼气可点燃煤炭,

口中喷出火焰;

22颈项强而有力,

恐惧在它前面开路;

23身上的皱褶紧密相连,

牢牢地密封在一起;

24心坚如石,

硬如磨石。

25它一站起来,勇士都害怕,

见它冲来,他们慌忙退缩。

26刀剑挡不住它,

长矛、标枪、尖戟也无能为力。

27它视铁如干草,

视铜如朽木。

28利箭吓不跑它,

弹石在它看来只是碎秸;

29棍棒无异于秸秆,

它嗤笑投来的标枪。

30它腹部有锋利的瓦片,

在淤泥上留下道道耙痕。

31它使深渊如锅翻腾,

大海如油锅滚动。

32它游过后留下一道波光,

使深渊仿佛披上银发。

33地上没有动物能与它相比,

像它那样无所畏惧。

34它藐视群雄,

在高傲的百兽中称王。”